ከ«ሙሴ ቀስተኛ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
No edit summary |
|||
መስመር፡ 1፦
[[ስዕል:Sebastiano Castagna.jpg|thumb|right|ሰላዩ ሙሴ ቀስተኛ]]
'''ሙሴ ቀስተኛ (ሴባስቲያኖ ካስታኛ)ጣልያንኛ፡ Sebastiano Castagna)''' ይሄ ሰው በ[[አድዋ ጦርነት]] የ[[ጣልያን]] መንግሥት አገራችንን [[ኢትዮጵያ]]ን በቅኝ ግዛትነት ለመግዛት ከገቡት ወታደሮች አንዱ ሲሆን፣ ለወረራ የመጣው የጠላት ኃይል በ[[ዳግማዊ ምኒልክ|ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ]] እና በሠራዊታቸው ቆራጥነት አድዋ ላይ ድል ሲሆን ተማርኮ የቀረና እስከ ዕለተ ሞቱ ድረስ ኢትዮጵያ ውስጥ የኖር ኢጣልያዊ ነው።
Line 25 ⟶ 26:
ሦስተኛውና የመጨረሻው ተልዕኮው በ [[ጥቅምት]] ወር [[1931|፲፱፻፴፩]] ዓ/ም ሲሆን [[በዳቄሮ]] በሚባል ሥፍራ ላይ ወደነበሩት ባላምባራስ (በኋላ ደጃዝማች) [[ገረሱ ዱኪ]] ነበር። እዚህ ሥፍራ ላይ ከሦስት ባላባቶች ጋራ የመጣው ቀስተኛ የሰባ አንድ ዓመት ሽማግሌ፣ ነጭ ጸጉር እና ባለሙሉ ጺማም ሲሆን አርበኞቹን ሰብስቦ በተጣራ አማርኛ ‘ንጉሠ ነገሥታችሁ እንኳን ትቷት የሄደውን አገር እናንተ በዚህ በልጅነት እድሜያችሁ ቅማል ወሯችሁ የማይቀርላችሁን ሞት ገደል ለገደል ከምታባርሩ ይልቅ ገብታችሁ ከኢጣልያ ጋር አገራችሁን በልማት ብታገለግሉ አይሻልም ወይ? መሣሪያችሁን አስረክባችሁ የገባችሁ እንደሆነ ኢጣልያ ትምራችኋለች፤ ሹመት እና ሽልማትም ትሰጣችኋለች” ብሎ ሲሰብካቸው ወጣት አርበኞቹም ቀደም ሲል በ፲፱፻፴ ዓ.ም ይኼው ሰላይ ወደ ራስ አበበ አረጋይ ዘንድ ሄዶ የጦሩን ኃይል ከሰለለ በኋላ ብዙ አርበኛ እንዳስፈጀ ሰምተው ስለነበር እነሱንም እንደዚሁ ለማስፈጀት እንደመጣ ተገንዝበውታል። ከሰበካው በኋላ ወደ እኩለ ቀን ሲሆን ተበተኑ።
[[ስዕል:Castagna on his last mission.jpg|left|thumb|የቀስተኛ (''በስተቀኝ በቡሽ ባርኔጣ'') መጨረሻ ይስለላ ተልዕኮ]]
ከዚህ በኋላ ሙሴ ቀስተኛ ወደሠፈረት ቦታ፣ በመጣባት በቅሎ በ[[ደጃዝማች ኪዳኔ ወልደመድኅን|ባሻ ኪዳኔ ወልደመድኅን]]ታጅቦ ሲሄዱ፣ ባሻ ኪዳኔ ቀስተኛ የለበሰው ካፖርት በደም እንዳይበላሽ በማሰብ
አንቶኒ ሞክለር (እንግሊዝኛ፤ Anthony Mockler) ስለቀስተኛ ሞት ሲያወሳን በስህተት በገረሱ ዱኪ ተሰቅሎ ሞተ ይለናል። ሆኖም የጣልያን መንግሥት ገረሱን ለሚገድልለት ሰው ፶ ሺህ ሊራ እንደሚሰጥ ማወጁንና በኋላ የጣልያን መንግሥት እንደራሴ፣ ዱካ ዳኦስታም ይሄንን ሽልማት እጥፍ እንዳደረገው ይነግረናል። <ref> Mockler(2003), p191</ref>
|