ከ«ፍኖተ ሰላም» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
Robot-assisted disambiguation: ብርቱካን - Changed link(s) to ብርቱካን (ፍሬ)
No edit summary
መስመር፡ 2፦
'''ፍኖተ ሰላም''' (ፍ/ሰላም) በ[[ኢትዮጵያ]] ውስጥ በ[[ጎጃም]] እምብርት ላይ የምትገኝ ከተማ ናት። ፍኖተ ሰላም ማለት መልካም መንገድ ወይም ጉዞ እንደማለት ሲሆን ይህንንም ስም ያወጡላት [[ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ]] እንደሆኑ ይነገራል። ጃንሆይ ከጣሊያን ጦርነት በኋዋላ ከስደት ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ አሁን ፍኖተ ሰላም ያለችበት ቦታ ላይ ከአጃቢዎቻቸው ጋር እረፍት ያደርጋሉ። እስከዚያን ጊዜ ድረስ ያደረጉት ጉዞም በሰላም የተሞላ ስለነበር ያንን ቦታ ፍኖተ ሰላም ብለው ሰየሙት። ከከተማዋ ወጣ ብሎ የሚገኝ አንድ የዋንዛ ዛፍ ይገኛል። ይህንንም የዋንዛ ዛፍ የተከሉት ንጉሱ ስለነበሩ እስካሁን ድረስ የአባ ንጉስ ዋንዛ እየተባለ ይጠራል።
 
ፍኖተ ሰላም በብዙ ነገር ትታወቃለች። በአካባቢው ያሉ ገበሬዎች [[ጤፍ]]፣ [[በቆሎ]]፣ [[ዳጉሳ]]፣ [[ኑግ]]፣ [[በርበሬ]] እና ሌሎችንም የእህል አይነቶች ያበቅላሉ። በፍራፍሬ [[ሎሚ]]፣ [[ብርቱካን (ፍሬ)|ብርቱካን]]፣ [[ፓፓዬ]] እንደልብ ይገኛል። በጣም ጥራት ያለው ቡና የሚገኝባት አገር ናት - ፍ/ሰላም። የባከል ቡና በጣዕሙ ይታወቃል። ከከተማው ወጣ ብሎ የገራይ የውሃ ግድብ ስለሚገኝ በተለይ በፆም ጊዜ እጅ የሚያስቆረጥም አሳ ይገኛል። ፍ/ሰላም በወተትና በማር ሀብትም በጣም የታውቀች ከተማ ናት። በከተማዋ አንድ ሁለተኛ ደረጃና አንድ መሰናዶ ትመሀርት በቶች አንዲሁም አንድ መምህራን ማሰልጠኛ ኮለጅ ይግኛሉ።
 
 
[[መደብ:የኢትዮጵያ ከተሞች]]