ከ«ግብረ ስጋ ግንኙነት» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
መስመር፡ 113፦
በሌሎች እንሥሣት፣ ነፍሳትንና አሦችን ጨምሮ፣ ሴቶቹ በአካል ከወዶቹ ይገዝፋሉ። ይህ ሁኔታ የድቀላ እንቁላልን ከማዘጋጀት ጋር የተያያዘ ነው ለማለት ይቻላል። ቀድም ሲል እንደተወሳው የእንስትን የዘር ቅንቁላል ወይንም ፍሬ ማዘጋጀት፣ የተባእትን የዘር ህዋስ ከማዘጋጅት ይልቅ ብዙ የንጥረነገር ቅምር ይጠይቃል። በአካል የገዘፉ እንስታን ብዙ የዘር እንቁላል መሥራት ይችላሉ። አንዳንድ ግዜ ይህ ፆታዊ የአካል ልዩነት እጅግ የበዛ ከመሆኑ የተነሳ ወንዶቹ የሴቶቹ ጥገኛ በመሆን ብቻ ተወስነው እንዲቀሩ ያደርጋል።
 
በአእዋፍ ውስጥ ወንዶቹ በአብዛኛው በህብረቀለም የተዋቡ (ለምሣሌ እንደ ተባእት የገነት ወፍ) ሆነው ይታያሉ። ይህ ሁኔታ አንዳንድ ፍጡራንን ለኑሮ በጂ ያልሁነ ሁኔታ ላይ ይጥላቸዋል የሚል አመለካከት አለ። (ለምሣሌ ህብራዊ ቀለም አንድን ወፍ ለአጥቂዎች በግልፅ እንዲታይ ያደርገዋል) ከዚህ በተፃፃሪነት ደግሞ የስንኩልነት መግለጫ (handicap principle)የሚባል አመለካከት አለ። ይህ አመለካከት ወንዱ ወፍ ራሱን ለአጥቂዎች አጋልጦ በመታየትበማሳየቱ፣ ነገዳዊ ጥንካሬውንና ድፍረቱን ለሴቶቹ ይገልፃል ይላል።
 
ሰብአዊ ፍጡራን፣ ወንዶቹ አጠቃላይ የሰውነት ግዝፈትና የሰውነት ፀጉር በመያዝ እንዲሁም ሴቶቹ ተለቅ ያሉ ጡቶችን በማውጣት፣ ስፋ ያሉ ዳሌዎችን በመያዝና ከፍ ያለ የውስጥ ሰውነት ቅባታዊ ይዘት በማፍለቅ የፆታ አካልዊ ልዩነትን ያሳያሉ።