ከ«የኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
መስመር፡ 1፦
'''የኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር''' የ[[ኢትዮጵያ]] (እንዲሁም በ[[ኤርትራ]] አብያተ ክርስትያናት) ዋና [[ካሌንደር]] ነው። አዲስ ዓመት በ[[ጁሊያን ካሌንደር]] አቆጣጠር በ[[ኦገስት]] 29 ወይም 30 የሚጀምር ሲሆን በ[[ግሪጎሪያን ካሌንደር]] ደግሞ ከ[[1901 እ.ኤ.አ.]] እስከ [[2099 እ.ኤ.አ.]] ድረስ በ[[ሴፕቴምበር 11]] ወይም 12 ይጀምራል። በየአራት ዓመቱ አንድ ቀን ይጨመራል። በአንድ ዓመት ውስጥ አስራ-ሁለት ባለሠላሣ ቀናት እና አንድ ባለ አምስት (ስድስት በአራት ዓመት) ቀናት ያሉባቸው ወራት አሉ።
 
በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ዓመታት ሁሉ በአራት መደባት ይዞራሉ፤ እነሱም ስለ ሐዋርያት ስሞች ዘመነ ማቴዎስ፣ ዘመነ ማርቆስ፣ ዘመነ ሉቃስ (ተጨማሪ የጳጉሜ ቀን የሚቀበለው) እና ዘመነ ዮሐንስ ይባላሉ።
 
የአመተ ምህረት ዘመናት ከጎርጎርዮስ 'አኖ ዶሚኒ' በ7 ወይም 8 አመታት የሚለይበት ምክንያት፣ ከ[[ኢየሱስ ክርስቶስ]] ልደት 400 አመት ያህል በኋላ [[አኒያኖስ እስክንድራዊ]] ዘመኑን ሲቆጥረው ትስብዕቱ በ[[መጋቢት 29]] [[1]] ዓ.ም. እንደ ሆነ ስለ ገመተ ይህ በ''ትስብዕት ዘመን'' 1ኛ አመት ሆኗል። ይህ አቆጣጠር በምሥራቅ ክርስቲያን አገራት ከተቀበለ በኋላም በ[[443]] ዓ.ም. ከ[[ሮማ]] [[ፓፓ]]ና ከምሥራቅ አቡናዎች መካከል ልዩነት ደርሶባቸው፤ በ[[517]] ሌላ መነኩሴ [[ዲዮኒሲዮስ ኤክሲጉዎስ]] ሌላ አቆጣጠር (''አኖ ዶሚኒ'') አቀረበ። በሱ ግምት ትስብዕቱ የተከሠተበት ቀን ከአኒያኖስ ግምት በፊት በ8 አመታት አስቀደመው። የ''አኖ ዶሚኒ'' አቆጣጠር በምዕራብ አውሮፓ ላይኛነት በማግኘቱ የትስብእት ዘመን 1 አመተ ምህረት በ''አኖ ዶሚኒ'' [[9 እ.ኤ.አ.]] ሆነ።