ከ«መጽሐፍ ቅዱስ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
መስመር፡ 7፦
 
== የመጽሐፍ ቅዱስ ልዩ ባህርያት ==
መጽሐፍ ቅዱስ የስነምግባር ጉዳዮችን በሚመለከት መመሪያ የሚሰጥ ከመሆኑም ሌላ እንደ ወንጀል፣ ረሃብና የአካባቢ መበከል ያሉት ችግሮች ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መፍትሔ የሚያገኙበትን መንገድ ይገልጻል። ችግሩ ግን፣ መጽሐፍ ቅዱስ እነዚህን ጉዳዮች አስመልክቶ የሚናገረውን ነገር ብዙ ሰዎች በቁም ነገር መመልከት ትተዋል። ከዚህ ቀደም ይህ መጽሐፍ ቢያንስ በምዕራቡ ዓለም እንኳ ትልቅ ተሰሚነት ነበረው። መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው በሰዎች አማካኝነት ቢሆንም እንኳ ቀደም ባሉት ጊዜያት በሕዝበ ክርስትና ውስጥ የነበሩት አብዛኞቹ ሰዎች የአምላክየ[[አምላክ]] ቃል መሆኑንና መልእክቱም አምላክ በመንፈስ አነሳሽነት ያስጻፈው እንደሆነ ያምኑ ነበር።
 
ይሁን እንጂ ዛሬ እያንዳንዱን ነገር መጠራጠር የተለመደ ነገር ሆኗል። ሰዎች ባህላቸውን፣ የተለያዩ ጽንሰ ሐሳቦችን፣ የስነምግባር ደንቦችንና የአምላክን መኖር እንኳ ሳይቀር የጠራጠራሉ። በተለይ የመጽሐፍ ቅዱስን ጠቃሚነት በተመለከተ ጥርጣሬ ገብቷቸዋል። አብዛኞቹ ሰዎች መጽሐፍ ቅዱስን ጊዜ ያለፈበትና አላስፈላጊ እንደሆነ አድርገው የሚያዩት ይመስላል። ከዘመናችን ምሁራን መካከል መጽሐፍ ቅዱስን እንደ አምላክ ቃል አድርገው የሚመለከቱት በጣም ጥቂት ናቸው። እንዲያውም አብዛኞቹ ሰዎች ከምሁሩ [[ጄምስ ባር]] አባባል ጋር ይስማማሉ፡- "ስለ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ልማዶች ያለኝ አመለካከት ''[[የሰው ልጅ]]'' የፈጠራ ውጤት ናቸው የሚል ነው። ''የሰው ልጅ'' የራሱን እምነት ያሰፈረበት መጽሐፍ ነው።"<ref>The Bible in the Modern World, By James Barr, 1973, p. 120</ref>
 
ይህ አመለካከት ወደ አንድ ነጥብ ያመራል፦ መጽሐፍ ቅዱስ ሰዎች የጻፉት ''ተራ'' መጽሐፍ ከሆነ ለሰው ልጅ ችግሮች ምንም ዓይነት ግልጽ የሆነ መልስ አይገኝም ማለት ነው። የሰው ልጆች በገዛ እጃቸው በሚያመጡት ጣጣ ከህልውናከ[[ህልውና]] ውጭ እንዳይሆኑ ወይም በኑክሊየርበ[[ኑክሊየር ጦርነት]] እንዳያልቁ አቅማቸው የፈቀደውን ያህል በጭፍን መዳከር ይኖርባቸዋል ማለት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ የአምላክ ቃል ከሆነ ግን ይህን አስቸጋሪ ጊዜ ለማለፍ የሚያስፈልገን ዋነኛው ነገር እርሱ ይሆናል።
 
የታሪክ መዝገቦች ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላሉ?
 
=== በብዛት በመሸጥ አቻ ያልተገኘለት ===
መጽሐፍ ቅዱስ በብዛት ታትሞ በመሸጥና በሰፊው በመሰራጨት ረገድ በሰው ዘር [[ታሪክ]] ውስጥ ቀዳሚውን ስፍራ ይዟል። ''[[ጊነስ ቡክ ኦቭ ወርልድ ሬኮርድስ]]'' የተባለው መጽሐፍ በ1988በ[[1988]] እትሙ እንደገለጸው ከ1815ከ[[1815]] እስከ [[1975]] ባሉት ዓመታት ውስጥ ብቻ ወደ 2.5 ቢልዮን የሚገመቱ ቅጂዎች ታትመዋል። ይህ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ነው። የመጽሐፍ ቅዱስን ያህል ሊሰራጭ ይቅርና ወደዚያ ቁጥር የተጠጋ አንድም መጽሐፍ በታሪክ አልታየም።
 
ከዚህም በተጨማሪ የመጽሐፍ ቅዱስን ያህል በብዙ ቋንቋዎች የተተረጎመ መጽሐፍ አይገኝም። ዛሬ መጽሐፍ ቅዱስ ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል ከ1800 በሚበልጡ የተለያዩ ቋንቋዎች ይገኛል። በኢትዮጵያበ[[ኢትዮጵያ]] እንኳን በአማርኛ፣በ[[አማርኛ]]፣ ትግሪኛ፣[[ትግሪኛ]]፣ ኦሮምኛ፣[[ኦሮምኛ]]፣ ወላይትኛ፣[[ወላይትኛ]]፣ ጉራግኛና[[ጉራግኛ]]ና ሌሎች ቋንቋዎች መጽሐፍ ቅዱስ በሙሉም ሆነ በከፊል ተተርጎሞ ይገናል። በአጠቃላይ ዛሬ 98 በመቶ ገደማ የሚሆነው የምድራችን ነዋሪ መጽሐፍ ቅዱስን በቋንቋው ማግኘት ይችላል።
 
=== ተደማጭነት ያለው መጽሐፍ ===
''[[ዘ ኒው ኢንሳይክለፒዲያ ብሪታኒካ]]'' መጽሐፍ ቅዱስን "በታሪክ ዘመናት ከታዩት ጽሑፎች ሁሉ ይበልጥ ተደማጭነት ያለው የመጻህፍት ስብስብ" ሲል ጠርቶታል።<ref>The New Encyclopæ̃diaEncyclopædia Britannica, 1987, Vol. 2, p.194.</ref> የ19ኛው [[ጀርመናዊ]] [[ባለቅኔ]] [[ሄንሪክ ሃይነ]] እንዲህ ብለዋል፦ "ይህን ሁሉ ማስተዋል ያገኘሁት ከአንድ መጽሐፍ ነው። . . . መጽሐፍ ቅዱስን በማንበብ። ቅዱስ መጽሐፍ መባሉ ይገባዋል። አምላኩን ያጣ ሰው ካለ በዚህ መጽሐፍ አማካኝነት ሊያገኘው ይችላል።"<ref>The Book of Books: An Introduction to Solomon Goldman, 1948, p. 219.</ref> በዚሁ መቶ ዘመን የኖረውና የጸረ-ባርነት እንቅስቃሴ አራማጅ የነበረው [[ዊልያም ኤች ሴዋርድ]] እንዲህ ብሏል፦ "የሰው ልጅ የመሻሻል ተስፋ የተመካው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በሚሄደው የመጽሐፍ ቅዱስ ተደማጭነት ላይ ነው።"<ref>The Book of Books: An Introduction, p. 222.</ref>
 
የዩናይትድየ[[ዩናይትድ ስቴትስ]] 16ኛ [[ፕሬዚዳንት]] የነበሩት [[አብርሃም ሊንከን]] መጽሐፍ ቅዱስን በሚመለከት እንዲህ ብለዋል፦ "አምላክ ለሰው ልጆች ከሰጠው ስጦታ ሁሉ የላቀ ስጦታ ነው። . . . መጽሐፍ ቅዱስ ባይኖር ኖሮ መልካሙንና ክፉውን ለይተን ማወቅ ባልቻልን ነበር።"<ref>Federal Register, Vol. 48, No. 26, February 7, 1983, p.5527</ref> የብሪታንያውየ[[ብሪታንያ]]ው የህግየ[[ህግ]] ሰው [[ሰር ዊልያም ብላክስተን]] "ሁሉም ሰብዓዊ ሕጎች የተመሰረቱት በእነዚህ ሁለት ሕጎች ማለትም በተፈጥሮ ሕግና አምላክ ለሰው ልጆች በሰጠው ሕግ [በመጽሐፍ ቅዱስ] ላይ ነው፤ እንግዲያው ሰብዓዊ ሕጎች ከእነዚህ ሕጎች ጋር እንዲጋጩ ማድረግ አይገባም ማለት ነው።"<ref>Chadman's Cyclopedia of Law, 1912, Vol. 1, pp. 86-91.</ref> ብለው ሲናገሩ መጽሐፍ ቅዱስ ምን ያህል ተደማጭነት እንዳለው ጎላ አድርገው ምግለጻቸው ነበር።
 
=== የተጠላና የተወደደ ===
በአንጻሩ ደግሞ በታሪክ ዘመናት ሁሉ የመጽሐፍ ቅዱስን ያህል የከረረ ተቃውሞ የገጠመው መጽሐፍ የለም። መጽሐፍ ቅዱስ ከመካከለኛውከ[[መካከለኛው ዘመን]] አንስቶ እስከ [[20ኛው መቶ ዘመን]] ድረስ በአደባባይ ተቆልሎ እንዲቃጠል ተደርጓል። በዛሬው ዘመን እንኳ ሳይቀር መጽሐፍ ቅዱስን በማንበባቸው ወይም በማሰራጨታቸው ምክንያት የገንዘብየ[[ገንዘብ]] ቅጣት የተጣለባቸው ወይም በእስራት የተቀጡ ሰዎች አሉ። ባለፉት መቶ ዘመናት እንዲህ ያለው "ወንጀል" ብዙውን ጊዜ አሰቃቂ ለሆነ ድብደባ አልፎ ተርፎም ለሞት የሚዳርግ ነበር።
 
መጽሐፍ ቅዱስ በሰዎች ውስጥ ያሳደረው [[ፍቅር]] ከዚሁ ጎን ለጎን የሚታይ ነው። ብዙዎች የማያቋርጥ ስደት ቢደርስባቸውም መጽሐፍ ቅዱስን ማንበባቸውን ገፍተውበታል። ለምሳሌ ያህል በ16ኛውበ[[16ኛው መቶ ዘመን]] የኖረውንና በኦክስፎርድበ[[ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ]] ተምሮ በካምብሪጅበ[[ካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ]] ውስጥ ትልቅ ቦታ ያለው አስተማሪ የነበረውን [[ዊልያም ቲንደልን]] እንመልከት።
 
ቲንደል ለመጽሐፍ ቅዱስ ከፍተኛ ፍቅር ነበረው። ይሁን እንጂ በዘመኑ የነበሩት ሃይማኖታዊ ባለ ሥልጣናት መጽሐፍ ቅዱስ ሙት በነበረው በላቲንበ[[ላቲን]] ቋንቋ ተወስኖ እንዲቀር ሽንጣቸውን ገትረው የሟገቱ ነበር። ቲንደል ግን የአገሩ ሶዎች መጽሐፍ ቅዱስን የማንበብ አጋጣሚ እንዲኖራቸው በማሰብ ወደ እንግሊዝኛ ቋንቋ ለመተርጎም ቆርጦ ተነሳ። ይህ ተግባሩ ከሕጉ ጋር የሚቃረን ስለነበር ቲንደል ጥሩ የማስተማር ስራውን ትቶ መሰደድ ግድ ሆነበት። የግሪክኛ ቅዱሳን ጽሑፎችን ("አዲስ ኪዳን") እና አንዳንዶቹን የዕብራይስጥ ቅዱሳን ጽሑፎች ("ብሉይ ኪዳን") ወደ አገሩ ቋንቋ ተርጉሞ እስኪጨርስ ኑሮውን በስደት ለመግፋት ተገዷል። ይሁን እንጂ በመጨረሻ በመያዙና መናፍቅ ነው ተብሎ በመወንጀሉ ተሰቅሎ እንዲሞትና በድኑም በእሳት እንዲቃጠል ተደርጓል።
 
ቲንደል፣ መጽሐፍ ቅዱስን ለማንበብ ወይም ለሌሎች ሰዎች እንዲዳረስ ለማድረግ ሲሉ ብዙ መሥዋዕትነት ከከፈሉት በርካታ ሰዎች መካከል አንዱ ብቻ ነው። ከሌላው ሰው የተለየ ምንም ነገር ያልነበራቸውን ብዙ ወንዶችና ሴቶች ይህን ያህል ድፍረት እንዲኖራቸው ያነሳሳ ሌላ መጽሐፍ በታሪክ ውስጥ አልታየም። ከዚህ አንጻር መጽሐፍ ቅዱስ በእርግጥም አቻ አይገኝለትም።