ከ«ጋኔን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 1፦
'''ጋኔን''' ወይንም '''አጋንንት''' የ[[እርኩስ መንፈስ]] አይነት ሲሆን ከ[[መጽሐፍ ቅዱስ]] ተመዘው በተስፋፉ ጽሑፎች ላይ የዚህ መንፈስ ታሪክ/አፈ-ታሪክ ተጽፎ ይገኛል። ለምሳሌ [[ቀኖናዊ]] ባልሆኑት ''[[ስነ ፍጥረት]]'' እና ''[[ሰይፈ ስላሴ]]'' በተባሉ የግዕዝ መጻሕፍት።
 
አሁንም ብዙው ህብረተሰብ እንዲህ ያስባል። በ[[መጽሐፍ ቅዱስ]] ስለሚጠቀሱ፣ እስካሁን ድረስ በዓለም ዙሪያ ያሉ [[አብያተ ክርስቲያናት]] ትንህርት እንዲህ ነው። አጋንንት የሳይንስ እውቀት ባላቸውም ሆነ በሌላቸው ኢትዮጵያውን ዘንድ እጅግ ከፍተኛ ፍርሃቻን የሚፈጥር አስተሳሰብ ነው። ነገር ግን የአጋንንት ታሪክ የሚመነጨው የ[[ሳይንስ]] አስተሳሰብ ባልተስፋፋበትና ስለ[[ቫይረስ]]ም ሆነ [[ጀርም]] በማይታወቅበት ዘመን ሲሆን ዘመናዊው የሳይንስ አስተሳሰብ ከዚህ ይለያል፣ እንደሚከተለው ይላል፦ ዋና ዓላማውም የበሽታዎችን አመጣጥ በሚያሳምን መልኩ ለመረዳት እና ለመተንበይ ነበር። ይሄ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በአብዛኛው ያልተማረ ህብረተሰብ የሚሰራበት የነበር ነው። ስለሆነም [[ሆድ ቁርጠት]]፣ [[ጉስምት]]፣ [[ብድብድ]] ወዘተ በአጋንንት ምክንያት የሚመጡ ተደርገው ይታሰቡ ነበር።
 
== የተለምዶ የአጋንንት አመጣጥ ታሪክ ==
እንደ መጽሐፎቹ''ሰይፈ ስላሴ'' ታሪክ፣ በሰማይ ቤት 100 የመላዕክት ነገዶች ነበሩ። ከለታት አንድ ቀን እግዚአብሔር በሌለበት፣ [[ሰባልስዮስ]] ወይንም [[ሰይፈ ስላሴ]] የተሰኘ የመላዕክት አለቃ እኔ ሁሉን ፈጠርኩ አለ። ከ100ዎቹ ነግዶች አንደኛው ወገን ይህን የሰባልስዮስን ቃል አመነ። ይሄው ቡድን ወደ እሳት ተጣለ። ከሳት ከወጣም በኋላ የሰይጣን አገልጋይ ሆነ፡፡ የነገዱ አባላቶችም መጠሪያ ስማቸውም አጋንንት ሆነ።
 
እንደዚሁ አፈ ታሪክ 99 የመላዕክት ነገዶች ስለቀሩ እግዚአብሔር 100ውን ለመሙላት [[አዳም]]ን ፈጠረ፡፡ ሆኖም አዳም ከ[[ጭቃ]] ስለተሰራ እና [[ሰይጣን]] ደግሞ ከ[[አየር]] እና [[ብርሃን]] ስለተሰራ፣ ሰይጣን ለሰው ልጅ ክብር መስጠት እምቢ አለ፣ ስለዚህም በሁለቱ መካከል የማያቋርጥ ጠብ አለ።