ከ«ጋኔን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
መስመር፡ 14፦
*በ''[[ኦሪት ዘዳግም]]'' 32፡15 ፣17 መሠረት በ[[ሙሴ]] መዝሙር፣ [[ይሹሩን]] (የ[[እስራኤል]] ሕዝብ መጠሪያ) እግዚአብሔርን ተወ፣ እግዚአብሔር ላልሆኑ አጋንንት እንደ ሠዉ ይጠቅሳል።
*በ''[[መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ]]'' 11፡14-15 [[ኢዮርብዓም]] ከ[[ይሁዳ]] ተለይቶ የእስራኤል ንጉሥ በሆነበት ጊዜ የ[[ይሖዋ]] ካህናት ትቶ ለራሱ አጋንንት ካህናት እንዳቆመ ይላል።
*በ''[[መዝሙረ ዳዊት]]'' 91፡6 በእግዚአብሔር መጠጊያ የሚኖር ሰው ልጅ «ከቀትር ጋኔን» እንደማይፈራ ያረጋግጣል። የጥንታዊ [[ግሪክ]] («ሳባ ሊቃውንት») ትርጉም እንዲህ ይላል፤ አሁን በይፋዊው ዕብራይስጥ ትርጉም ግን «በቀትር ከሚያጥፋው ጥፋት» እንደማይፈራ ይላል።
*በ''[[መዝሙረ ዳዊት]]'' 95፡5 የአረመኔ ጣኦታት ሁሉ ለአጋንንት እንደ ሆኑ ይገልጻል።
*በ''መዝሙረ ዳዊት'' 105፡35-7 እስራኤላውያን የአሕዛብ እምነቶች ሲከተሉ እንኳን ልጆቻቸውን ለአጋንንት እንደ ሠዉ ይነግራል።
*በ''[[ትንቢተ ኢሳይያስ]]'' 13፡21 የ[[ባቢሎን]] ውድቀት ሲነበይ አጋንንት በዚያ ይዘፍናሉ ይላል። (በአንዳንድ ትርጉም ግን «አጋንንት» የሚለው የ[[ዕብራይስጥ]] ቃል ደግሞ [[ፍየል]] ማለት ሊሆን ይችላል።)