ከ«አሙን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
ጥNo edit summary |
ጥ sp |
||
መስመር፡ 5፦
በግብጻውያን ሃይማኖት፣ አሙን ያልተወለደ ያልተፈጠረ ፈጣሪ መሆኑ ይታመን ነበር። ከ1550 ዓክልበ. የገዙት ፈርዖኖች በተለይ ያከብሩት ነበር። በጊዜ ላይ፣ የአሙን እና የ[[ፀሐይ]] ጣኦት [[ራ]] መታወቂያዎች አንድ ሆነው ስያሜው «አሙን-ራ» ይባል ጀመር። በ1360 ዓክልበ. ያህል ግን ፈርዖኑ [[4 አመንሆተፕ]] የራሱን ስም ወደ «አከናተን» ቀይሮ የአሙን አምልኮት ከለከለው፤ በፈንታውም የ[[አተን]] እምነት እንዳቆመ ይታወቃል። አከናተን በ1345 ዓክልበ. ግድም በሞተበት ወቅት፣ የአሙን-ራ ቄሳውንት ተነሥተው ሃይማኖታቸውን መለሡ፤ ስለዚህ የአከናተንም ልጅና ተከታይ ቱታንካተን ስሙን ወደ [[ቱታንካመን]] ሊቀይር ተገደደ።
በ[[ኩሽ መንግሥት]]፣ በ[[ኖባ]] እና በ[[መርዌ]] አሙን «አማኔ» ተብሎ በተለይ
በሊቢያ የአሙን መቅደስ በበረሃ ውስጥ በ[[ሲዋ ኩሬ]] ይገኝ ነበር። ግሪኮቹም ወዲህ ተጒዘው በየጊዜ ያማክሩት ነበር። የአሞን መቅደሶች ደግሞ በግሪክ አገር ሠሩ። ዲዮዲሮስ የሊቢያ [[አፈ ታሪክ]] ሲተርክልን፣ ሃሞን በ[[አፍሪካ]] (በ[[ኒሳ]] ደሴት በ[[ትሪቶን]] ወንዝ) የገዛ ንጉሥ ነበረ፤ ሚስቱም [[ሬያ]] ነበረች። የሬያ ወንድም [[ክሮኖስ]] ግን ከ[[ቲታኖች]] ጋራ ወርሮ ሊቢያንም ሬያንም ከሃሞን እጅ ያዘ። ከዚህ በኋላ የሃሞን ልጅ [[ባኩስ]] ወይም [[ዲዮኒሶስ]] ክሮኖስን አሸነፈው፤ የክሮኖስና የሬያንም ልጅ [[ዩፒተር ኦሊምፑስ]]ን ማርኮ እርሱን የግብጽ አገረ ገዥ አደረገው።
|