ከ«ሙሴ ቀስተኛ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
ጥ Robot-assisted disambiguation: ግሪክ - Changed link(s) to ግሪክ (አገር) |
No edit summary |
||
መስመር፡ 1፦
'''ሙሴ ቀስተኛ
ሙሴ ቀስተኛ በ[[1860|፲፰፻፷]] ዓ/ም በ[[ሲሲሊ]] ደሴት አይዶኔ በሚባል ሥፍራ ተወለደ። ስለልጅነት ዘመኖቹ እና በወጣትነቱም የ[[ጣልያን]]ን የጦር ሠራዊት እንዴት እና ለምን እንደተቆራኘ መቼ፣ ከማን ሠራዊት ጋር፣ የትኛው ወደብ ላይ ኢትዮጵያ ላይ ለመዝመት እንደመጣ በእርግጠኛነት ባይታወቅም፤ ድሉ የ[[ኢትዮጵያ]] ሆኖ ሙሴ ቀስተኛ በምርኮኛነት በ[[ዳግማዊ ምኒልክ|ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ]] ሠራዊት እጅ ወደቀ። ከተማረከም በኋላ በፈቃዳቸው እዚያው ኢትዮጵያ ውስጥ ከቀሩት ብዙ ጣልያኖች አንዱ እንደነበረና በተግባረ ዕድ ሞያው ታዋቂነትን አትርፎ በምህንድስና ተግባራት እንደተሰማራና ኢትዮጵያም ውስጥ እስከ ሁለተኛው የ[[ፋሽስት ኢጣልያ]] ወረራ ድረስ ኖሯል። በወረራውም ጊዜ የጣልያንን ጦር ዓለቆች በሰላይነት እንዳገለገላቸውና በመጨረሻም በአንድ ቆራጥ ኢትዮጵያዊ [[አርበኛ]] እጅ ሕይወቱን እንዳጣ ስለእሱ ከተጻፉ ጥቂት ታሪካዊ መሥመሮች ላይ እንገነዘባለን።
|