ከ«ሙሴ ቀስተኛ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
Robot-assisted disambiguation: ግሪክ - Changed link(s) to ግሪክ (አገር)
መስመር፡ 11፦
‘የባሕላዊ ቅርስ ሽግግር’ በካዛንችስ፣ አዲስ አበባ የታሪካዊ ቤት አርዕያዊ ጥገና’ (እንግሊዝኛ “Cultural Heritage Promotion” An exemplary restoration of a historic building in Kasainchis, Addis Abeba, Ethiopia (Addis Abeba November 2005) በሚል ዕትም ላይ በሠፊው፤- በአድዋ ጦርነት ተማርከው ወደ አዲስ አበባ የመጡት የጣልያን ወጥቶ አደሮች አብዛኞቹ በግንባታ እና የመንገድ ሥራ መስክ ተሰማርተው እንደነበር ይገልጽና ሙሴ ቀስተኛም ከነዚህ አንዱ እንደነበር ያረጋግጥልናል።
 
ይኼው ዕትም ሙሴ ቀስተኛ [[የካቲት፳፫]] ቀን [[1904|፲፱፻፬]] የተመረቀውን የ[[ገነተ ጽጌ መናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ]] ቤተ ክርስቲያንን ዕቅድ የነደፈው መሐንዲስ እንደነበረ እና በ[[1930|፲፱፻፴]] ዓ/ም የታተመው “በምሥራቅ አፍሪቃ የጣልያን ግዛት” መምሪያ (ጣልያንኛ፣ guida del’Africa Orientale Italiana, Milano, Consociazione Turistica Italiana, 1938) ሕንጻውን በማሞገስ እንደተነተነው አስቀምጦታል።<ref> “Cultural Heritage Promotion” An exemplary restoration of a historic building in Kasainchis, Addis Abeba, Ethiopia (Addis Abeba November 2005) p12</ref> ሆኖም የቤተ ክርስቲያኑን ዕቅድ የነደፈው መሐንዲስ የ[[ግሪክ (አገር)|ግሪክ]] ተወላጁ እንደነበረና ሙሴ ቀስተኛ የቤተ ክርስቲያኑን ግንባት ተኮናትሮ የሠራ እንደሆነ ሌሎች ታሪካዊ ዘገባዎች ይገልጻሉ። ቀስተኛ ከዚህም ሕንጻ ሌላ በ[[1902|፲፱፻፪]] ዓ/ም የተመረቀውን ዘመናዊ የ'አቢሲኒያ ባንክ' ሕንጻ [[ኢጣልያ]]ዊው መሐንዲስ ቫውዴቶ (Vaudetto) ባዘጋጀው ንድፍ መሠረት ሙሴ ቀስተኛ እንደሠራው [[ሪቻርድ ፓንክኸርስት]] ዘግቦታል።
 
==የፋሽሽት ወረራ ዘመን==