ከ«አሹር (ከተማ)» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
r2.7.1) (ሎሌ መጨመር: als, ar, az, ca, cs, de, eo, es, eu, fi, fr, he, hr, hu, it, ja, ka, ko, ku, mn, nl, no, pl, pt, ro, ru, sh, sk, sr, sv, tr, uk, vi, zh
No edit summary
መስመር፡ 1፦
'''አሹር''' የ[[አሦር]] ጥንታዊ ዋና ከተማ ነበር። ፍርስራሹ በ[[ጤግሮስ ወንዝ]] ምዕራብ ዳርቻ አሁን ሊታይ ይችላል። «አሹር» የሚለው ስም ደግሞ በ[[አካድኛ]] (አሦርኛ) ማለት የአገሩ አሦር ስም እና የ[[አረመኔ]] ሃይማኖታቸው ዋና ጣኦት [[አሹር (ጣኦት)|አሹር]] ነበር። በ[[ዕብራይስጥ]]ም «አሹር» ማለት ወይም አገሩ ወይም [[አሦር (የሴም ልጅ)|አሦር]] (የ[[ሴም]] ልጅ) ሊሆን ይቻላል።
 
አሹር ከተማ የተሠራው ከ2400 ዓክልበ. አስቀድሞ ይሆናል። በ1980 ዓክልበ. ገደማ ጥንታዊው የአሦር ንጉሥ [[ኡሽፒያ]] የአሹር ቤተ መቅደስ መስራች እንደ ነበር ይተረካል። በዚህ ወቅት አሹር የአሦር ከተማ-አገር መቀመጫ ሆነ። [[1 እሽመ-ዳጋን]] በ1678 ዓክልበ. ከሞተ በኋላ የ[[ባቢሎን]] ንጉሥ [[ሃሙራቢ]] ሥልጣን ያዘ፤ የአሹር ነገሥታት ለትንሽ ጊዜ ለባቢሎን ተገዥ ቢሆኑም በይፋ በነፃነት ገዙ። ከ1440 ግድም አሹር በ[[ሚታኒ]] ንጉሥ [[ሻውሽታታር]] ተዘርፎ ከዚያ እስከ 1366 ዓክልበ. ድረስ የአሹር ነገሥታት ለሚታኒ ይገዙ ነበር። በ1366 ዓክልበ. ግን [[1 አሹር-ኡባሊት]] የሚታኒ ሰዎችን አባረራቸውና የአሦር መንግሥት ይስፋፋ ጀመር። በ[[ኒኑርታ-አፒል-ኤኩር]] ዘመን (በ1195 ዓክልበ. ገደማ)፣ አንድ [[የምድር መንቀጥቀጥ]] በአሹር የነበረውን መቅደስ በሙሉ አጠፋው።

በ887 ዓክልበ. [[2 አሹር-ናሲር-ፓል]] የአሦርን ዋና ከተማ ከአሹር ወደ [[ካልሁ]] አዛወረው። የአሦር መንግሥት በ622 ዓክልበ. በወደቀበት ጊዜ የአሦር ጠላቶች ባቢሎን፣ [[ሜዶን]]ና [[እስኩቴስ]] ሰዎች አሹርን አጠፉት። ሆኖም በኋላ አዲስ መንደር በሥፍራው ቆሞ እስከ [[14ኛው ክፍለ ዘመን]] ዓ.ም. ድረስ ይቆይ ነበር።
 
[[መደብ:አሦር]]