ከ«ሰብታ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 3፦
በአንዳንድ ሊቃውንት ዘንድ፣ ሰብታ በ[[አረቢያ]] ዳርቻ (በ[[ቀይ ባህር]] ላይ) ይገኝ የነበረው [[ሳቦታ]] በተባለ ሥፍራ ሰፈረበት። ይህ ሳቦታ የ[[ሃስረሞት]] ዋና ከተማ ነበረች። ሌላ ሊቃውንት እንደሚያስቡት፣ በ[[ሞሮኮ]] ዳርቻ (በ[[ጂብራልታር ወሽመጥ]] ላይ) የሚገኘው [[ሴውታ]] የሰብታ ልጆች መኖራያ ይሆናል። በዚህ ሃሣብ ልጆቹ በሳህራ በረሃ ሠፈሩ።
 
ዳሩ ግን በ[[1ኛው ክፍለ ዘመን]] የጻፈው አይሁዳዊ መምህር [[ፍላቭዩስ ዮሴፉስ]] እንዳለው፣ «የሰብታ ልጆች [[ግሪክ|ግሪኮች]] አሁን አስታቦራውያን የሚሏቸው ናቸው።» በጥንት «አስታቦራስ» ማለት አሁን በ[[ሱዳን]]ና በ[[ኢትዮጵያ]] [[አትባራ ወንዝ]] የሚባል ስለ ሆነ፣ የሰብታ ኩሽ ልጆች በዚያ እንደ ሰፈሩ አመለከተ። በልማዳዊ መዝገብ የተወረሰው [[የኢትዮጵያ ነገሥታት ዝርዝር]] ደግሞ ሰብታ ለ30 አመታት በ[[ኩሽ መንግሥት]] ላይ ንጉሥ ሆነ ይላል፤ ይህም ከ[[ካም]]፣ ኩሽና ሃባሢ በኋላ ሲሆን አመቶቹ ሲቆጠር ምናልባት ከ2259 እስከ 2229 ዓክልበ. ይሆናል። በ[[አኒዩስ]] ባሳተመ በአንዱ አፈ ታሪክ ዘንድ፣ ይህ የኩሽ ልጅ ሰብታ (ወይም «ሳባትዮስ ሳጋ» ተብሎ) ከዚያ ዘመን በፊት በ[[ሳካ]]ዎች ([[እስኩቴስ]]) ላይ የነገሠ ሲሆን፣ ከዚያም ዘመን በኋላ ከአፍሪካ ወደ [[ጣልያን]] ሂዶ በዚያው አገር ደቡብ ክፍል ነገሠ። ከዚህ በላይ [[ሳጉንቶ]] ከተማ በ[[እስፓንያ]] እንደ መሠረተ የሚል ልማድ አለ።
 
[[መደብ:የኢትዮጵያ ነገሥታት]]