ከ«ሰብለ ወንጌል» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
ጥ Robot-assisted disambiguation: የመን - Changed link(s) to የመን (አገር) |
No edit summary |
||
መስመር፡ 1፦
[[ስዕል:Libnadengel.jpg|300px|right|thumb| የንግስት ሰብለ ወንጌል ባል የነበሩት አጼ [[ልብነ ድንግል]] ]]▼
▲ንግስት '''ሰብለ ወንጌል''' የዓፄ [[ልብነ ድንግል]] ሚስት ስትሆን ከእናት ንግስት [[እሌኒ]] ሞት በሁዋላ በኢትዮጵያ ውስጥ የእሌኒን እግር ተክታ ከፍተኛ ተሰሚነት የነበራት ናት። በነበረችበት ዘመን፣ የ[[አህመድ ግራኝ]] ጦር በ[[ቱርክ]] ጠመንጃ አንጋቢወች ታግዞ ብዙ የኢትዮጵያን ክፍል በተቆጣጠረበት ዘመን ነው። በዚህ የጦርነት ዘመን የመጀምሪያ ልጇ ሲገደል አራተኛው ልጇ ፣ የወደፊቱ [[አጼ ሚናስ]] ተማርኮ ወደ [[የመን (አገር)|የመን]] ተግዟል። ይህ የተማረከው ልጇ በሁዋላ በእስረኞች ቅይይር ተመልሷል። ሰብለ ወንጌል የአዳሎችን ጦር እስከመጨረሻው የታገለችን ባሏ በ[[ደብረ ዳሞ]] ([[ትግራይ]]) በ1540 በህመም ከሞተ በኋላ ሁሉ እጅ ሳትሰጥ ታግላ አታግላለች።
ከባሏ ሞት ኋላ ሁለተኛ ልጇ አጼ [[ገላውዲወስ]] ንጉስ ሆነ። ይህ ልጇ በደቡብ ክፍል ውጊያ ከፍቶ በመታገል ላይ እያለ በ[[ክሪስታቮ ደጋማ]] የሚመራው የ[[ፖርቹጋል]] ጦር [[ምጽዋ]] ላይ አረፈ። ይህ የሆነው እቴ ሰብለ ወንጌል [[ደብረ ዳሞ]] ተራራ ላይ ለአንድ አመት እጅ ሳትሰጥ በአህመድ ግራኝ ተከባ ከተቀመጠች በኋላ ነበር። ከተራራው ምሽጓ ላይ
የንግስቲቷን ድጋፍ ተከትሎ የአካባቢው ህዝብ ለፖርቹጋሎቹ ምግብና እርዳታ እንዳደረገ ይዘገባል። ብዙወችም ይህን ሰራዊት እንደተቀላቀሉ ይነገራል። ቁስለኛውን በማከም፣ የለበሰችውንም ጥምጣም በመቅደድ ባንዴጅ በመስራት፣ ለሞቱትም በማልቀስ በጦር ውሎው ሁሉ ተሳታፊ ነበረች። በ1543 የክሪስታቮና የገላውዲወስ ሃይሎች ተገናኝተው በማበር አህመድ ግራኝን አሸነፍው ገደሉት። የግራኝ ሚስት [[ባቲ ድል ወምበሬ]] ብታመልጥም ልጇ መሃመድ ግን ተማርከ።
በዚህ ጊዜ የልጇን የ[[ሚናስ]]ን መፈታት ከ[[ድል ወምበሬ]] ጋር በመልዕክተኛ ለመወያየት ችላለች። ሚናስ በዚህ ጊዜ ለቱርኩ መሪ [[ሱልጣን ሱሊማን]] በየመን ተልኮ
ከ6 አመት ጦርነት በኋላ [[ገላውዲወስ]] ተገደለና [[ሚናስ]] ስልጣን ላይ ወጣ። ለሚቀጥሉት 4 አመታት፣ እንደቀደመችው [[ንግስት እሌኒ]] በመንግስቱ ውስጥ ከፍተኛ ተሰሚነትን አገኘች። ቀጥሎም በ[[ካቶሊክ]] እና በ[[ኦርቶዶክስ]] ሃይማኖት መካከል በተነሳው ሽኩቻ የኦርቶዶክስ ሃይማኖትን በመደገፍ በጽናት ቆማለች። ይሁንና በዚህ ምክንያት በተነሳው ጸብ የፖርቹጋል ካቶሊኮች ሊገደሉ ሲሉ በማማለድ ስራ ጉዳት እንዳይደርስባቸው አድርጋለች። [[ቤርሙዴዝ]] የተባለው ታውቂው የፖርቹጋል ተጓዥም ንጉሱን ገላውዲወስን በማናደዱ ከመገደል የተረፈው በሰብለ ወንጌል ተራዳኢነት ነበር። የስፔኑ ጀስዊት ፓትሪያርክ [[ኦቨዶ]]ም ከሞት የተረፈው በንግስቲቱ ምክንያት ነበር። [[ሠርፀ ድንግል]]ን ወደስልጣን እንዲወጣም ከጦረኞቹ በላይ ያገዘችው እናት ንግስት ሰብለ ወንጌል ነበረች። ይህ ምርጫዋም ጥበብ የተሞላበት ነበር ምክንያቱም ሰርጸ ድንግል ለ34 አመት ሲገዛ አገሪቱን በመከላከል ወደ ሰላም አሸጋግሯል። <ref>ሪታ ፓንክኸርስት http://www.oneworldmagazine.org/focus/etiopia/women2.html</ref>
ሰብለ ወንጌል በአጼ[[ሠርፀ ድንግል]] ዘመን፣ በ1560 ዓ.ም. [[አመድ በር]] በተባለ ቦታ አረፈች።
አጼ [[ልብነ ድንግል]] የራሱንና የሰብለ ወንጌልን ምስሎች የ[[ክሪት]] ሠዓሊ በመቅጥር ካሳለ በኋላ [[ግብጽ]] ወደ ሚገኘው [[ቅዱስ አትናቲዮስ ገዳም]] (st antony monastery) እንዳስላከው ተመዝግቦ ይገኛል <ref>Abstracts of papers - Byzantine Studies Conference, Volumes 16-19 (1990)</ref>። የአጼ ልብነ ድንግል ምስል ከዚሁ ገዳም ይመነጫል።
==ማጣቀሻወች ==
<references/>
[[መደብ : ሰብለ ወንጌል]]
|