ከ«ጋሜር» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
ሎሌ መጨመር: bg:Гомер
No edit summary
መስመር፡ 10፦
 
[[እስላም]] ጸሓፊው [[አል ታባሪ]] (905 ዓ.ም. ግድም) ስለ ጎሜር ዕድሜው እስከ ሺህ አመት ድረስ እንደ ደረሰ የሚል የፋርስ ልማድ ተረከ።<ref>Tabari, ''Prophets and Patriarchs'' (Vol. 2 of ''[[History of the Prophets and Kings]]'')</ref>
 
በ[[1490]] ዓ.ም. [[አኒዩስ ዴ ቪቴርቦ]] የተባለ ጣልያናዊ መነኮሴ ባሳተመው ዜና መውዋዕል ዘንድ፣ የ[[ባቢሎን]] ታሪክ ጸሓፊ [[ቤሮሶስ]] (290 ዓክልበ.) ስለ ኖኅ ልጆች ብዙ መዝገቦች አቅርቦ ነበር። በዚህ በኩል፣ በ[[ናምሩድ]] 10ኛው ዓመት የያፌት ልጅ «ኮሜሩስ ጋሉስ» (ጋሜር) የሰፈረበት አሁን [[ጣልያን]] የተባለው ሀገር ሆነ። ከ30 ዓመት በኋላ ግን ሌሎች ከዚህ ኮሜሩስ ዘር በ[[ባክርቲያ]] እስከ [[ጋንጄስ]] ወንዝ ድረስ ሠፈሩ። ከዚህም እንደገና 20 አመት በኋላ፣ ኮሜሩስ የ[[ሠረገላ]]ና የ[[ጋሪ]] ዕውቅት ከእስኩቴስ ተመልሶ ወደ ጣልያን አስገባ። ከዚያም 8 ዓመት በኋላ ልጁ [[ኦኩስ ዌዩስ]] እንደ ተከተለው ይባላል። በተጨማሪ የ[[ሳርማትያ]]ና የ[[ጀርመን]] መስራች [[ቱዊስኮን]] ሲሆን፣ በአንዳንድ ጸሄፊ ዘንድ የሱ መታወቂያና የጋሜር ልጅ አስከናዝ አንድላይ ነው። ዘሬ ግን አብዛኛው መምህሮች የአኒዩስን ጽሑፍ እንደ ሐሣዊ መረጃ ይቆጥሩታል።
 
የጋሜር ልጆች የወለዷቸው ወገኖች መታወቂያ በተለያዩ ምንጮች ዘንድ እንዲህ ነው፦