ከ«ጉታውያን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 5፦
መጀመርያ በታሪክ መዝገብ የሚታዩ፣ ለ[[አዳብ]] ንጉሥ ለ[[ሉጋል-አኔ-ሙንዱ]] መንግሥት (2100 ግ.) ግብር ከሚከፍሉ ሕዝቦች መካከል ሲዘረዝሩ ነው። በጽላት መዝገብ ዘንድ አገራቸው ከ[[ሹቡር]] ደቡብና ከ[[ኤላም]] ስሜን ይገኛል። በአካዳውያንም ዘመነ መንግሥት፣ ለንጉሥ [[ታላቁ ሳርጎን]] (2060 ግ.) ተገዥ ሁነው ከ[[ሉሉቢ]] ብሔር አጠገብ ነበሩ።
 
በ2013 ዓክልበ. ግ. የአካድ ምጉሥ [[ሻርካሊሻሪ]] የጉቲዩምን ንጉሥ ሻርላግን ማረከው፤ በ2010 ግ. «ቀንበር (ግብር) በጉቲዩም አደረገበት» ይዘገባል። የአካድ መንግሥት ግን ከዚያ ድካም ለመሆን ሲጀምር፣ ጉታውያን በሜስጶጦምያ ላይ ብዝበዛ ያድርጉ ነበር። ሠራዊት እንደ ደረሰባቸው ግን ሸሽተው ነበር። ከቤት ማለፍ ወይም እንኳን በእርሻ መግባት አስጊ ሁኔታ ስለ ሆነ፣ የሜስጶጦምያ ምጣኔ ሀብት ተበላሸና ራብ ሆነ። በመጨረሻ፣ (2002 ግ.) ጉታውያን አካድን ወረሩና ገዙት። እንዲሁም የጉቲ ሠራዊት [[ኡሩክ]]ንና ኤላምን የዛኔ ወረሩ። የጉታውያን ንጉሥ [[ኤሪዱፒዚር]] እራሱን እንደ አካድ ነገስታት በማምሰል፣ ማዕረጉ 'የጉቲ ንጉሥና የ4 ሩቦች ንጉሥ' ተባለ። ጉታውያን በአገሩ ሁሉ የታሰሩት እንስሶች ከጉረኖአቸው ፈቱ። የጉታውያን ግዛት ለ[[እርሻ ተግባር]]ም ሆነ ለዜና መዋዕል ዝገባ ጥንቁቅ አልነበረም። በ''[[ሱመራዊው ነገሥታት ዝርዝር]]'' በአንዳንድ ቅጂ 25 ዓመታት ብቻ እንደ ገዙ የሚለው አቆጣጠር ትክክል ይመስላል፤ በትንሽ ጊዜ ውስጥ አገሩ በጽኑ ረሃብ ተያዘ። የኤላም ንጉሥ [[ኩቲክ-ኢንሹሺናክ]] ከጉታውያን ዘመን በፊትና በኋላ ስለሚታወቅ ለ124 አመታት (እንደ ሌላ ቅጂ) ሊሆን አይችልም።
 
በ1977 ዓክልበ. ያሕል፣ የኡሩክ ንጉሥ [[ኡቱ-ኸንጋል]] የጉታውያን ንጉሥ [[ቲሪጋን]]ን እንዳሸነፈ ጉታውያንንም ከአገራቸው እንዳስወጣ ይባላል። ከዚህ በኋላ በ1964 ዓክልበ. የ[[ኡር]] [[ኡር-ናሙ]] ጉቲዩምን ዘረፈው። በ1669፣ 1667ና 1662 ዓክልበ. የ[[ባቢሎን]] ንጉሥ ሃሙራቢ ጉቲዩምን እንደገና ድል አደረገው።