ከ«የካቲት ፮» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
አዲስ ገጽ ፈጠረ፦ «'''የካቲት ፮'''፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፻፶፮ ኛው ዕለት ሲሆን፤ የበጋ ወቅት ፵፩ ኛው ...» |
(No difference)
|
እትም በ05:05, 22 ጃንዩዌሪ 2011
የካቲት ፮፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፻፶፮ ኛው ዕለት ሲሆን፤ የበጋ ወቅት ፵፩ ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፪፻፲ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፪፻፱ ቀናት ይቀራሉ።
ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች
- ፲፭፻፶፭ ዓ/ም - የ ፲፪ ዓመቱ ወጣት ሠርጸ ድንግል አባታቸው አጼ ሚናስ ሲሞቱ በስመ መንግሥት መለክ ሰገድ ተብለው ነገሡ። ከመንገሣቸው በፊት ማር (ጌታ) ሠርፀ ድንግል ይባሉ የነበር። ሥራቸውን የሚሠሩት በእናታቸው በእቴጌ አድማስ ሰገድ ሥሉስ ኃይላ አማካይነት ነበር፡፡
ልደት
ዕለተ ሞት
- ፲፭፻፶፭ ዓ/ም ኢትዮጵያን ከአራት ዓመታት በንጉሥነት የመሯት አፄ ሚናስ (ስመ መንግሥት፣ ቀዳማዊ አድማስ ሰገድ) በዕለተ እሑድ አረፉ፡፡ አጼ ሚናስ የአጼ ገላውዴዎስ ወንድምና የአጼ ልብነ ድንግል ልጅ ነበሩ።
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም የቀድሞዋ ኮንጎ ሊዮፖልድቪል (የአሁኗ የኮንጎ ሪፑብሊክ) የመጀመሪአው ጠቅላይ ሚኒስትር ፓትሪስ ሉሙምባ መገደላቸው ይፋ ተደረገ።
ዋቢ ምንጮች
- መርስዔ ኀዘን ወልድ ቂርቆስ፤ ዕለታዊ የታሪክ ድርጊት “የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የመጀመሪያው ፓትረያርክ” (፲፱፻፶፩ ዓ/ም)፣
የኢትዮጵያ ወራት | |
---|---|
መስከረም - ጥቅምት - ኅዳር - ታኅሣሥ - ጥር - የካቲት - መጋቢት - ሚያዝያ - ግንቦት - ሰኔ - ሐምሌ - ነሐሴ - ጳጉሜ |