ከ«ጥገኛ አምክንዮ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
No edit summary |
|||
መስመር፡ 22፦
== ሙሉ ማብራሪያ ==
*« ነገ ዝናብ ''ከ'''ዘነበ ስራ አልመጣም።»
:: ነገ ዝናብ ቢዘንብና ስራ ባልመጣ፣ እውነት ነኝ።
:: ነገ ዝናብ ቢዘንብና ስራ ብመጣ፣ ውሸት ነኝ።
:: ነገ ዝናብ ባይዘንብና ስራ ብመጣ -- እንዲሁም
:: ነገ ዝናብ ባይዘንብና ስራ ብቀር፣ ዝናብ ሳይዘንብ የማደርገውን ስላልተናገርኩ በሁለቱም አቅጣጫ ውሸታም ነህ የሚለኝ አይኖርም። ዝምታ በአምክንዮ እውነት ስለሆነ፣ ቀዳሚው አረፍተ ነገር ሃሰት እስከሆነ ድረስ፣ እውነት ነኝ።
የ'''ጥገኛ አምክንዮ''' ከዕለት ተለት አምክንዮአችን ለየት ያለ የሥነ-አምክንዮ ምርምር ውጤት ነው። ስለሆነም ለመረዳት ምሳሌና ጥንቃቄ የተመላበት ምርምር ያስፈልጋል። የጥገኛ አምክንዮ አመጣጥን በምሳሌ ለመመርመር እሚከተለውን እንመልከት
* መሰረት አዲስ አበባ ውስጥ አለች፣ [[ስለዚህ]] መሰረት ኢትዮጵያ ውስጥ አለች።
:እንግዲህ የጥገኛ አምክንዮ ይህን መሰረታዊ እውነታ በመቀበል የሚነሳ የአምክንዮ አይነት ነው። '''መሰረት አዲስ አበባ ውስጥ አለች" የሚለው ክፍል [[ቀዳሚ አረፍተ ነገር]] ሲባል መሰረት ኢትዮጵያ ውስጥ አለች የሚለው [[ተከታይ አረፍተነገር]] ነው። እዚህ ላይ፣ ከላይ እንዳስተዋልነው፣ ቀዳሚው አረፍተ ነገር ውሸት ቢሆን እንኳ ሙሉው አረፍተ ነገር ምንጊዜም እውነት እንደሆነ እንረዳለን። ስለሆነም የጥገኛ አምክንዮ ዋጋ ከነባራዊው አለም እውነታ ተነጥሎ መታየት አለበት። ይህን በቀላሉ ለመረዳት ሌላ ምሳሌ እነውሰድ፦
|