ከ«ጥር ፲፫» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
መስመር፡ 1፦
[[1533|፲፭፻፴፫]] ዓ/ም - መስከረም ፭ ቀን - ኀሙስ ሞተ አጼ ልብነ ድንግል በደብረ ዳሞ እንዘ መዋዕለ መንግሥቱ ፴ወ፪ቱ ዓመት። ፴ወ፫ ዕለታት ወነግሠ ወልዱ ገላውዴዎስ ዘስመ መንግሥቱ አፅራር ሰገድ፤ እንዘ መዋዕሊሁ ፲ወ፰ ዓመት።
[[ጥር 13|ጥር ፲፫]] ቀን፣
በ[[ኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር]] የዓመቱ ፻፴፫ ኛው ዕለት ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነ [[ዮሐንስ]] ፪፻፴፫ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ [[ማቴዎስ]]፤ [[ማርቆስ]] እና [[ሉቃስ]] ደግሞ ፪፻፴፪ ዕለታት ይቀራሉ።
 
=[[ታሪካዊ ዓመት በዓላት ወይም ማስታወሻዎች|ታሪካዊ ማስታወሻዎች]]=
 
*[[1864|፲፰፻፷፬]] ዓ.ም.፣ ደጃዝማች ካሳ ምርጫ (አባ በዝብዝ) በ[[አክሱም ጽዮን ማርያም]] ቤተ ክርስቲያን ስመ መንግሥታቸው "ዮሐንስ ራብዓዊ" ([[ዮሐንስ ፬ኛ]]) ተብሎ፣ በጳጳሱ በብፁዕ አቡነ አትናቴዎስ እጅ ተቀብተው በሥርዓተ መንግሥት ንጉሠ ጽዮን፣ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ተብለው ነገሡ። በታሪክ እንደተመዘገበው በዚሁ ንግሥ ምክንያት ሦስት ቀን በዓል ሆኖ፣ ለግብር ፬ ሺህ ሰንጋ ታርዶ፣ ፶ ጉንዶ ማር የፈጀ፣ ፻፶ ሺህ ገንቦ ጠጅ ቀርቦ፣ በደስታ ሲበላ ሲጠጣ ሰንብቷል።
 
*[[1933|፲፱፻፴፫]] ዓ/ም የ[[ፋሺስት ኢጣሊያ]]ን ሠራዊት ጠራርጎ ለማስወጣት የተቀጣጠለውን ዘመቻ ከፍጻሜ ለማድረስ ከ[[ሱዳን]] ድንበር ወደ [[ኢትዮጵያ]] የዘለቁት [[ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ]]፣ አርበኞችና የ[[እንግሊዝ]] ጦር፣ በ[[ኦሜድላ]] ላይ አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ የሆነውንና የይሁዳ አንበሳ ከመሐሉ የሚገኝበት የ[[ኢትዮጵያ]] ሰንደቅ ዓላማን ተከሉ፤ አውለበለቡ።
 
*[[1944|፲፱፻፵፬]] ዓ.ም. ለ[[አዲስ አበባ]] ሕዝብ የውሃ አገልግሎት የሚሰጠው የ[[ገፈርሳ]] ግድብ በ[[ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ]] ተመረቀ።
 
*[[1954|፲፱፻፶፬]] ዓ.ም. [[ኢትዮጵያ]] ሦስተኛውን የአፍሪቃ እግር ኳስ ውድድር የ[[ግብፅ]]ን ቡድን አራት ለ ሁለት አሸንፋ ዋንጫውን ተሸለመች።
 
=ልደት=
 
=ዕለተ ሞት=
 
 
 
 
==ዋቢ ምንጮች==
 
* ሪፖርተር፣ ኪንና ባህል - “ሳምንቱ በታሪክ”
 
 
 
 
[[መደብ:ዕለታት]]