ከ«ዳግማዊ ዓፄ ኢያሱ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
መስመር፡ 33፦
ጀመረ። በ[[ላስታ]]ና በ[[ሸዋ]] እንዲሁም በ[[ትግሬ]] (የ[[ራስ]][[ስሁል ሚካኤል]] መነሳት) ጠንካራም ባይሆን በለሆሳስ ራስ ገዝነት የመጀመረው በዚህ ንጉስ ጌዜ ነበር። የንጉሱ የቀደመ ሙሉ ሃይል በ[[ጎንደር]]ና [[ጎጃም]] ተወስኖ ነበር<ref>[[Edward Ullendorff]], ''The Ethiopians: An Introduction to Country and People'', second edition (London: Oxford Press, 1965), p. 81</ref>።
 
[[ስዕል:Mentewab.jpg|left|200px|thumb| እቴጌ ምንትዋብ]] እቴጌ ምንትዋብ ከአማቷ፣ ሮማነወርቅ( የአጼ [[በካፋ]] እህት) ፣ ልጅ [[ምልማል እያሱ]] ጋር የምታደርገውም ግንኙነት ዳግማዊ እያሱን እጅግ ያስቆጣ ነበር። እቴጌ ምንትዋብ ከዚህ ከምልምል እያሱ ዘንድ 3 ልጆን ሴት ልጆችን ስታፈራ ከነዚህ ውስጥ አንዷ [[ወይዘሮ አስቴር ኢያሱ]] በመባል በቁንጅናዋ በታሪክ የምትታወቀው ነበረች። የእቴጌ ምንትዋብ ከአማቷ ልጅ ጋር መማገጥ በዘመኑ እጅግ ትልቅ ነውር የነበር ቢሆንም ንጉሱ ግማሽ እህቶቹን ይንከባከብ ነበር። አባታቸውን ግን ከመጥላቱ የተነሳ በ1742 ዓ.ም (እ.ኤ.አ) ከ[[ጣና]] ሃይቅ ዳርቻ ካለ ገደል ተወርውሮ እንዲሞት እንዳደረገ ይታመናል.<ref>[[ተክለ ጻድቅ መኩሪያ]]፣ [[የኢትዮጵያ ታሪክ ከአጼ ልብነ ድንግል እስከ አጼ ቴዎድሮስ]]፣ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት</ref> ።
 
== ሞት ==
[[ስዕል:Mentewab.jpg|left|200px|thumb| እቴጌ ምንትዋብ]]ዳግማዊ እያሱ ግንቦት 1755 ላይ በጸና ታመው በሚቀጥለው ወር ሞቱ። የምልማል እያሱ እህት በወንድሟ ሞት ንዴት መርዝ ሰጥታው እንደገደለቸው በጊዜው የታመነ ጉዳይ ነበር። እቴጌ ምንትዋብም ልጇን ለማስቀበር ከ[[ግምጃ ቤት]] ንዋይ ብትፈልግ ከጥቂት ዲናሮች በስተቀር ካዝናው ባዶ ሆኖ ተገኘ። በዚህ ያዘነቸው ምንትዋብ ሁሉን ትታ በ[[ቁስቋም]] ወዳሰራችው ቤተመንግስቷ ሄዳ ከጎንደር ለመራቅ ዛተች። ሆኖም ግን ጥቂት መኳንንት የልጅ ልጇ [[ኢዮአስ]] እንደራሴ ሆና እንድትቀጥል አሳመኗት።<ref>The Royal Chronicle of his reign is translated in part by Richard K. P. Pankhurst, ''The Ethiopian Royal Chronicles'' (Addis Ababa: Oxford University Press, 1967).</ref>
 
== ማጣቀሻ ==