ከ«ጎልጎታ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
አዲስ ገጽ ፈጠረ፦ «'''ጎልጎታ''' በአዲስ ኪዳን ወንጌሎች መሰረት ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት ቦታ ስም ነ...»
 
No edit summary
መስመር፡ 1፦
'''ጎልጎታ''' በ[[አዲስ ኪዳን]] [[ወንጌል|ወንጌሎች]] መሰረት በ[[ኢየሩሳሌም]] አካባቢ [[ኢየሱስ ክርስቶስ]] የተሰቀለበት ቦታ ስም ነው። ይህ ቦታ በዮሐንስ 19፡20 «ለከተማ ቅርብ ነበረ» ሲባል እንዲሁም በዕብራውያን 13፡12 «ከበር ውጭ» መሆኑን ይመሰክራል።
 
በአራቱ ወንጌሎች ሁሉ ስለ ስፍራው ተመሳሳይ ታሪክ አለ፦
መስመር፡ 13፦
በ[[ሉቃስ ወንጌል]] ያለው ስም '''ቀራንዮም''' ከ[[ግሪክ (ቋንቋ)|ግሪኩ]] ቃል Κρανίον /ክራኒዮን/ (የራስ ቅል) ደረሰ። ነገር ግን «ጎልጎታ» የሚለው ስም ዕብራይስጥ ሳይሆን የ[[አራማያ]] ቃል «ጉልጋልታእ» (የራስ ቅል) ይመስላል።
 
አዲስ ኪዳን ከ[[ኢየሩሳሌም]]ከኢየሩሳሌም በር ውጭ እንደ ነበር ምንም ቢገልጽም፣ በ[[317]] ዓ.ም. የ[[ሮሜ]] ንጉሥ [[ቆስጠንጢኖስ]] እናት [[ቅድስት ሄሌና]] ወደ ከተማው ሄዳ፣ የዛኔ በከተማው ውስጥ የ[[አረመኔ]] ጣኦት ቤተ መቅደስ በሆነበት ስፍራ ጎልጎታን እንዳገኘች ገመተች። ከዚያ ጀምሮ ሄሌና ያገኘችው ኮረብታ እንደ «ጎልጎታ» ሆኖ ከብሯል። ይህ ቦታ ከ[[ደብረ ጽዮን]] (ከሰሎሞን ቤተ መቅደስ) ወደ ምዕራብ ቢገኝ፣ በዚያ ዘመን የኖረው ክርስቲያን ጸሐፊ [[አውሳብዮስ]] ግን ጎልጎታ ከደብረ ጽዮን ወደ ስሜን ይገኛል ብሎ ጻፈ።<ref>አውሳብዮስ፣ ''ኦኖማስቲኮን'' 365.</ref> ስለዚህ ሄሌና ያመለከተችው ኮረብታ በእውኑ ጎልጎታ መሆኑ አጠያያቂ ሆኗል።
 
ከዚህ በላይ ከኢየሩሳሌም በር ውጭ ወደ ስሜን በኩል ሌላ ኮረብታ «የራስ ቅል ኮረብታ» ይባላል፤ ይህም ኮረብታ የ[[ጭንቅላት]] ቅርጽ አለው። ስለዚህ ከ[[19ኛው ክፍለ ዘመን]] ጀምሮ ያው ወደ ስሜን የሚሆነው ኮረብታ በእውነት ጎልጎታ ነው ያሚያስቡ ጥቂቶች አይደሉም።