ከ«ሥልጣኔና እንጉርጉሮው» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
መስመር፡ 3፦
'''ሥልጣኔና እንጉርጉሮው''' በስነ-ልቡና ተመራርማሪው [[ሲግመንድ ፍሩድ]] በ1929 ዓ.ም. የተጻፍ እንዲሁም በ1930 ዓ.ም በ[[ጀርመንኛ]] የታተመ መጽሃፍ ነው። ከፍሩድ ስራወች ዋና ከሚባሉት ወገን ሲሆን በምዕራቡ አለም ከፍተኛ ተነባቢነት ያለው መጽሃፍ ነው።.<ref>Harv|Gay|1989|loc=p. 722</ref>
 
ግለሰቦች በስልጣኔ ላይ ያንጎራጉራሉ የዚህ ምክንያቱ በአንድ ግለሰብና በስልጣኔ መካከል የማያባራ ቅራኔ በመኖሩ መሆኑን ፍሩድ አሰፈረ። የዚህ ቅራኔ መሰረታዊ መንሴ ግለሰቦች በደመነፍስ ነጻነትን ሲፈልጉ ስልጣኔ ግን ከያንዳንዱ ግለሰብ መታዘዝንና እራስን መግዛት ይጠይቃል። የሰው ልጅ በራሱ አረመኒያዊ የሆኑ የደመነፍስ ፍላጎቶች አሉት (ለምሳሌ የመግደል፣ የማያልቅ የፍትወተ ስጋ ፍላጎት ወዘተ...) ። ነገር ግን እኒህ ደመነፍስ ፍላጎቶች በማህበራዊ ኑሮ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳሉ። ስለሆነም በማናችውም የታሪክ ዘመናት የተፈጠሩ ስልጣኔወች የሰውን ልጅ ደመነፍስ ፍላጎት ለማቀብ ህግ አውጥተዋል። አትግደል፣ አትድፈር፣ አታመንዝር፣ የሌላ ሰውን ሃብት አትውሰድ ወዘተ... የሚሉ ህጎች ወጥተው ህጎቹን የተላለፈ ከፍተኛ ቅጣት በዘመናትና በስልጣኔያት ሁሉ ሲቀጣሲቀበል ይታያል። ይህ እንግዲህ፣ በፍሩድ አስተሳሰብ፣ በስልጣኔ ውስጥ የሚንሸራሽሩ ዜጎች በስልጣኔ ላይ የማያባራ ቅሬታ እንዲያበጁ አድርጓል።
 
ከላይ የተጻፈው የፍሩድ ርዕዮተ አለም መሰረቱ የሰው ልጅ አንድ አንድ በተፈጥሮ ያሉት ምንጊዜም የማይቀየሩ የደመነፍስ ባህርዮች ናቸው። ከነዚህ የሰው ልጅ መሰረታዊ ባህርዮች ፍሩድ ዋና ያላቸው፦ ፍትወተ ስጋ የመፈለግ ባህርይና አንድ ግለሰብ ይህን ፍላጎት እንዳያሟላ ከላይ ሆነው የሚከለክሉትን የበላዮች (ባለ ስልጣናት፣ አለቆች፣ አዛዦች..ወዘተ..)ና በፍትወት ስጋ ተፎካካሪወች ላይ ጥል ለመፍጠር ያለ የደመነፍስ ባህርይ ናቸው።