ከ«ሙሴ ቀስተኛ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
No edit summary |
No edit summary |
||
መስመር፡ 1፦
'''ሙሴ ቀስተኛ ((ሴባስቲያኖ ካስታኛ)ጣልያንኛ፡ Sebastiano Castagna)''' ይሄ ሰው በ[[አድዋ ጦርነት]]
ሙሴ ቀስተኛ
ይሄ ሰው በአገራችን የታሪክ ዘገባዎች ላይ፣ ምናልባትም በታሪካችን ላይ በተጫወተው ሚና ረገድ በቂም ባይሆንም፣ ‘ብቅ፣ ጥልቅ’ እያለ ሲመዘገብ እናገኘዋለን። ስለዚህ ሰው አሟሟት ፀሐፊው በልጅነት ዘመን ያጠናው በመሆኑ ስለሰውዬው ማንነት እና አመጣጥ ለመመርመር ላደረገው ጥረት መነሻ ነው።
Line 9 ⟶ 7:
==ከአድዋ ድል መልስ==
ፔጎሎቲ የሚባል ጸሐፊ “ኢጣልያዊው በንጉሥ ምኒልክ ቤተ መንግሥት” (“Un Italiano alla Corte di Menelik,” Storia Illustrata 148 (March 1970): 79-85.) በተሰኘው መጽሐፉ ላይ ሙሴ ቀስተኛ በ[[ፋሽሽት ኢጣልያ]] ሁለተኛ የሙከራ ጊዜ ፣ በአድዋ ጦርነት ላይ የተሳተፈ አዛውንት እንደነበረና [[አዲስ አበባ]] ላይ በተግባረ ዕድ ችሎታው በ[[ዳግማዊ ምኒልክ]] እንዲሁም [[ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ]] ተወዳጅነትን እንዳፈራ ይዘግብና ለጥቆም በ ‘ሕዝብ ሥራ ሚኒስቴር’ ውስጥ ዲሬክቶር ሆኖ ይሠራ እንደነበር፣ በተለይም የ[[ደስታ ዳምጠው|ራስ ደስታ ዳምጠው]]ን አክስት ካገባ በኋላ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ምን ያህል አክብሮት እንዳገኘ ይነግረናል። <ref> Pegolotti (1970): pp 79-85.</ref> በትውልድ አገሩ አይዶኔ ደግሞ ስለእሱ የታተመ ጽሑፍ ላይ አንጀላ ሪታ ፓሌርሞ ከዚሁ ከወይዘሮ በላይነሽ ጋብቻ ማሪያ እና ጁሴፒና የተባሉ ሁለት ሴት ልጆች እንደተወለዱለት ታበሥራለች። <ref> www.quiaidone.it/giornalino/Gennaio2009.pdf sebastiano castagna</ref>
‘የባሕላዊ ቅርስ ሽግግር’ በካዛንችስ፣ አዲስ አበባ የታሪካዊ ቤት አርዕያዊ ጥገና’ (እንግሊዝኛ “Cultural Heritage Promotion” An exemplary restoration of a historic building in Kasainchis, Addis Abeba, Ethiopia (Addis Abeba November 2005) በሚል ዕትም ላይ በሠፊው፤- በአድዋ ጦርነት ተማርከው ወደ አዲስ አበባ የመጡት የጣልያን ወጥቶ አደሮች አብዛኞቹ በግንባታ እና የመንገድ ሥራ መስክ ተሰማርተው እንደነበር ይገልጽና ሙሴ ቀስተኛም ከነዚህ አንዱ እንደነበር ያረጋግጥልናል።
|