ከ«ጾመ ፍልሰታ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 11፦
እመቤታችን ከአባቷ ከኢያቄም እና ከናቷ ከሐና [[ነሐሴ 7|ነሐሴ ፯]] ቀን ተጸንሳ [[ግንቦት 1|ግንቦት ፩]] ቀን በ[[ሊባኖስ]] ተወልዳለች:: <እምሊባኖስ ትወጽዕ መርአት :- ከሊባኖስ ሙሽራ ትወጣለች > እንደተባለ :: እምቤታችን በእናት አባቷ ቤት ሦስት ዓመት፤ በቤተ መቅደስ አሥራ ሁለት ዓመት፤ ከልጇ ከወዳጇ ከ[[ኢየሱስ ክርስቶስ]] ጋር ሠላሳ ሦስት ዓመት ከ ሦስት ወር : ከ[[ዮሐንስ ወልደዘብዴዎስ]] ዘንድ አሥራ አራት ዓመት ከ ዘጠኝ ወር ቆይታ በ ፷፬ ዓመት ዕድሜዋ በ [[49|፵፱]] ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች:: የእመቤታችንን ስም የሚገልጹ የውዳሴ ጽሑፎችም በእድሜዋ ልክ ተደርሰዋል። ለምሳሌ የ[[ውዳሴ ማርያም]] ቁጥር ፷፬ ነው፤ የ[[መልክአ ማርያም]] ቁጥርም ፷፬ ነው።<ref> ሥርዓተ አምልኮ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ http://ethiopianorthodox.org/amharic/archivee/seasonal/filsetapict.pdf</ref>
 
ባረፈች ጊዜ ቅዱሳን ሐዋርያት ተሰባስበው አስከሬኗን ይዘው ወደ ጌቴሴማኒ መቃብር ለማሳረፍ ሲሄዱ አይሁድ ለተንኮል አያርፉምና ተተናኮሏቸው:: ቀድሞ ልጇ ሞቶ ተነሳ፣ አረገ እያሉ ሲያስቸግሩን ይኖራሉ: ደግሞ አሁን እሷም ተነሳች፣ አረገች ሊሉ አይደል በማለት አይሁድ ተሰባስበው አስከሬኗን ለማቃጠል ሲተናኮሉ [[እግዚአብሔር]] በተአምር ከነዚያ አይሁዶች አድኗቸዋል :: የእመቤታችንንም አስከሬን ነጥቆ ከሐዋርያው ከ[[ቅዱስ ዮሐንስ]] ጋር በገነት በዕፀ ህይወት ስር አኑሯቸዋል :: ከዚያ በኋላ ሐዋርያት ሥጋዋን አግኝተው ይቀብሩት ዘንድ በአረፈች በ ስምንተኛው ወር ከነሐሴ ፩ ጀምሮ እስከ ነሐሴ ፲፬ ቀን ድረስ ሁለት ሱባዔ ይዘው በ አሥራ አራተኛው ቀን ሥጋዋን ከጌታ ተቀብለው በጸሎትና በምህላ በፍጹም ደስታ በጌቴሰማኔ አሳረፉት :: በ ሦስተኛውም ቀን ተነስታ ስታርግ ከሰኡቃዊያን ወገን የሆነው ሐዋርያው [[ቅዱስ ቶማስ]] አያት:: እርሱም በቀብር ስርዓቱ ጊዜም አልነበረም:: ሀገረ ስብከቱ [[ህንድ]] ስለነበር ሊያስተምር ወደዛው ሂዶ ነበርና:: በዚያም ሲያስተምር ሰንብቶ በደመና ተጭኖ ሲመጣ ያገኛታል:: ትንሳኤዋን ከርሱ ሰውራ ያደረገች መስሎት አዝኖ "ቀድሞ የልጅሽን ትንሳኤ ሳላይ ቀረሁ አሁን ደግሞ ያንቺን ትንሳኤ ሳላይ ቀርቼ ነውን ?" ብሎ ቢያዝንባት እመቤታችንም ከርሱ በቀር ማንንም ትንሳኤዋን እንዳላየ ነግራ አጽናናችው:: ለሌሎቹ ሐዋርያትም እንዲነግራቸው ለምልክትም /ለምስክርም እንዲሆነው ሰበኗን /መግነዟን ሰጥታው አረገች:: ቶማስም [[ኢየሩሳሌም]] ደርሶ ሐዋርያትን "የእመቤታችን ነገርስ እንደምን ሆነ?" ሲል ቢጠይቅ "አግኝተን ቀበርናት እኮ" አሉት:: እርሱ ምስጢሩን አዉቆ ደብቆ "ሞት በ[[ጥር]] በነሐሴበ[[ነሐሴ]] መቃብር" እንዴት ይሆናል ? አይደረግም ይላቸዋል:: ሊያሳያቸውም መቃብሩ ዘንድ ሂደው ቢከፍቱት አጧት:: እርሱም "አታምኑኝም ብዬ እንጂ እርሷስ ተነስታ አርጋልች" በማለት ሁኔታውን ተረከላቸውና ለምስክር ይሁንህ ብላ የሰጠችውን ሰበኗን አሳያቸው:: ከዚህ በኋላ ለበረከት ይሆናቸው ዘንድ ሰበኑን ተካፍለው ወደየአህገረ ስብከታቸው ሄዱ:: ዛሬ በቅዳሴ ጊዜ ዲያቆኑ በሚይዘው የመጾር መስቀል ላይ በሁለት ቀዳዳዎች አልፎ ተጠምጥሞ የምናየው መቀነት መሰል ጨርቅ የዚያ ሰበን ምሳሌ ነው::ነው።
 
በዓመቱ ሐዋርያት ከያሉበት ተሰባስበው ቶማስ ትንሳኤሽን አይቶ እኛስ እንዴት ይቀርብናል ብለው ከነሐሴ ፩ ቀን ጀምርው ሱባዔ ቢይዙ ከሁለት ሱባዔ በኋላ እንደገና ትንሳኤዋንና እርገቷን ለማየት በቅተዋል:: ሐዋርያዊት የሆነች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናም ምእመኖቿ ከእመቤታችን በረከትን እንዲያገኙ ይጾሙ ዘንድ ይህን ሐዋርያት የጾሙትን ጾም እንዲጾሙ አዉጃለች:: ምእመናንም በተለየ መልኩ በጾም በጸሎት በሱባዔ ጽሙድ ሆነው ይህን ወቅት ያሳልፋሉ::ያሳልፋሉ።
 
የእመቤታችን ትንሳኤ ድንገት እንደእንግዳ ደራሽ እንደ ዉሀ ፈሳሽ የተደረገ ሳይሆን በቅዱሳት መጻሕፍት በትንቢተ ነቢያት የተገለጸ ነው:: ነቢዩ ዳዊት በመዝሙር ፻፴፩ ቁጥር ፲ ላይ "አቤቱ ወደ እረፍትህ ተነስ አንተና የመቅደስህ ታቦትም" ይላል:: በዚህም ምዕመናንን ወደ ምታሳርፍበት ወደ መንግሥተ ሰማያት የመቅደስህ ታቦት ድንግል ማርያምን ይዘህ ተነስ አለ:: ታቦት የጽላት ማደርያ እንደሆነ ሁሉ እምቤታችንም ለክርስቶስ ማደርያ በመሆኗ አማናዊት ታቦት ትባላለች::ትባላለች።
 
ንጉስ [[ሰሎሞን]]ም በ[[መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን]] ምዕራፍ ፪ ቁጥር ፲ ላይ "ውዴ እንዲህ ብሎ ተናገረኝ፤ ወዳጄ ሆይ ተነሽ: ውበቴ ሆይ ነይ" ብሏል:: እዚህ ላይ "ወዳጄ ...ዉበቴ " የተባለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት ::
ክቡር ዳዊት መዝሙር ፵፬ ቁጥር ፱ ላይ "በወርቅ ልብስ ተጎናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች" እንደሚል ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለም ቤዛነቱን ከፈጸመ በኋላ ወደ ቀደመ ክብሩ እንዳረገ እመቤታችን ቅድስት ድንገል ማርያምም በቀኙ ትቀመጥ ዘንድ " ተነሽ ነይ" አላት :: እንግዲህ ይህንና የመሰለዉን ሁሉ ይዘን የእናታችንን እረፍቷን ትንሳኤዋን እንዘክራለን እንመሰክራለንም::እንመሰክራለንም።
 
 
==ዋቢ ምንጮች==
<references/>