ከ«ሙሴ ቀስተኛ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
መስመር፡ 17፦
==የፋሽሽት ወረራ ዘመን==
 
በ[[ጥቅምት]] ወር [[1928|፲፱፻፳፰]] ዓ/ም ወረራው ሲጀመር የኢትዮጵያ ወጥቶ አደሮች እና አርበኞች የጠላትን ጦር ለመከላከል በሰሜን፤ በደቡብ፤ በምሥራቅ እና በምዕራብ ግንባሮች ተሠማርተው የተቻላቸውን ያህል ተቋቋሙ። ሆኖም የፋሽሽት ሠራዊት በዘመናዊ መሣሪያ እና የመርዝ ቦንብ አይሎባቸው በግንባር ለግንባር ግጥሚያ ይሸነፉና ንጉሠ ነገሥቱም በ[[ግንቦት]] ወር ተሰደው ወደ [[እንግሊዝ]] አገር ሄዱ። አገሪቷም በጣልያን ቁጥጥር ስር አደረች። የ[[ግራዚያኒ]] ሠራዊት ግን በ[[ደቡብ]] ግንባር [[ደስታ ዳምጠው|ራስ ደስታ ዳምጠው]] እና [[ደጃዝማች በየነ መርዕድ]] ፤ በ[[ምዕራብ]] የባላምባራስ [[ገረሱ ዱኪ]] አርበኞች በሰሜን [[ሸዋ]] ደግሞ የ[[ራስ አበበ አረጋይ|ራስ አበበ አረጋይ]] ሠራዊት አልበገር ብለው አስቸግረውት ቆዩ።
 
ግራዚያኒ በድርድር እነኚህን መሪዎች ለማስገባት ባደረገው ጥረት መልእክተኛና ሰላይ አድርጎ የመረጠው የኢትዮጵያውያንን ባህል ለ አርባ ዓመታት ያጠናውንንና የራስ ደስታን አክስት ያገባውን ይሄንኑ ሙሴ ቀስተኛን ነበር።