ከ«ደጋ እስጢፋኖስ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 1፦
'''ደጋ እስጢፋኖስ''' በ[[ጣና]] ሃይቅ ውስጥ በሚገኘው [[ደጋ ደሴት]] ውስጥ የሚገኝ ቤ/ክርስቲያን ሲሆን ወደ200 የሚጠጉ መነኮሳትን ያስተዳድራል። ቤ/ክርስቲያኑ የተቆረቆረው በ13ኛው ክፍለ ዘመን፣ በአጼ [[ይኩኖ አምላክ]] የወንድም ልጅ በ[[ሂሩተ አምላክ]] ነበር። ሂሩተ አምላክ ከአቡነ [[ተክለ ሃይማኖት]] ጋር በወሎ በሚገኘው [[ሃይቅ እስጢፋኖስ]] በአስተማሪያቸው [[እየሱስ ሞዓ]] የተማሩ የአንድ ክፍል ሰወች ናቸው።
 
ቀደምቱ ደጋ እስጢፋንኖስ በ19ኛው ክፍለ ዘመን በእሳት ሲቃጠል አሁን የቆመው ቤ/ክርስቲያን በምትኩ ተሰርቷል። በዚህ ምክንያት ከታሪክ አንጻር የቤ/ክርስቲያኑ ዋና መስዕብ ሆኖ የሚቀርበው ሳይቃጠል የተረፈው ሙዚየሙቤተ-መዘክሩ ነው። በዚህ ሙዚየምመዘክር የ[[ይኩኖ አምላክ]]፣ [[ቀዳማዊ ዳዊት]]፣ [[ዘርአ ያዕቆብ]]፣ [[ዘድንግል]]፣ [[ፋሲለደስ]]ና [[ባካፋ]] የደረቁ ቅሬቶች ይገኛሉ። አጼ [[ሃይለ ስላሴ]] በ1951 ደሴቲቱን ከጎበኙ በኋላ የነገስታቱ እሬሳ በመስታውት ሳጥን እንዲቀመጥ አደርጉ። የፋሲለደስ ቅሪት ከሌሎቹ ነገስታት በበለጠ መልኩ እስካሁን ብዙ ሳይበላሽ በመቆየቱ የፊቱን መልክ ከቅሪቱ መገንዘብ አሁን ድረስ ይቻላል።