ከ«ኤንመርካር» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 1፦
'''ኤንመርካር''' በ[[ሱመር]] (ሳንጋር) ነገስታት ዝርዝር ዘንድ የ[[ኡሩክ]] (ኦሬክ) ከተማ መስራች ነበረ። በዚያ ዝርዝር ጽህፈት 420 (ወይም በሌላ ቅጂ 900) ዓመታት እንደ ነገሰ ይላል። ደግሞ አባቱ የ[[ኡቱ]] ልጅ [[መስኪያግካሸር]] ወደ ባሕር ገብቶ ኤንመርካር መንግስቱን ከ[[ኤአና]] ከተማ እንዳመጣ ይጨምራል።
 
የኤንመርካር ስም በሌላ የሱመር ጽሑፍ ደግሞ ተገኝቷል። ''[[ኤንመርካርና የአራታ ንጉስ]]'' በተባለው ተረት እሱ የኡቱ ልጅ ይባላል። (ኡቱ በሱመር እምነት የ[[ጸሓይ]] አምላክ ነበር።) ይህ ተረት የሰው ልጅ ልሳናት መደባለቁን ይናገራል። ኡሩክን ከመመስረቱ በላይ ታላቅ መስጊድ በ[[ኤሪዱ]]ም እንዳሰራ ይተረታል። ለመሆኑም፣ አራታ እንዲገዛለት የሚለው መልእክት በአፍ መናገር ስለሚከብድ፣ ኤንመርካር ጽሕፈት በሸክላ ጽላት ላይ መጻፍ እንደ ፈጠረ ይላል።
 
በተጨማሪ በዚሁ ጽሑፍ ኤንመርካር የዙሪያው አገሮች ልዩ ልዩ ልሳናት እንደገና አንድ እንዲሆኑ ይጸልያል። እነዚህ አገራት [[ሹቡር]]፣ [[ሐማዚ]]፣ [[ሱመር]]፣ ኡሪ-ኪ (የ[[አካድ]] ዙርያ) እና [[አሞራውያን|የማርቱ አገር]] ናቸው።