ከ«ኤንመርካር» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 1፦
'''ኤንመርካር''' በ[[ሱመር]] (ሳንጋር) ነገስታት ዝርዝር ዘንድ [[ኡሩክ]] (ኦሬክ) ከተማ የመሰረተመስራች ነበር፤ በዚያ ዝርዝር ጽህፈት 420 ዓመት እንደ ነገሰ ይላል። ደግሞ አባቱ የ[[ኡቱ]] ልጅ [[መስኪያግካሸር]] ወደ ባሕር ገብቶ ኤንመርካር መንግስቱን ከ[[ኤአና]] ከተማ እንዳመጣ ይጨምራል።
 
የኤንመርካር ስም በሌላ የሱመር ጽሑፍ ደግሞ ተገኝቷል። ''[[ኤንመርካርና የአራታ ንጉስ]]'' በተባለው ተረት እሱ የኡቱ ልጅ ይባላል። (ኡቱ በሱመር እምነት የ[[ጸሓይ]] አምላክ ነበር።) ይህ ተረት የሰው ልጅ ልሳናት መደባለቁን ይናገራል። ኡሩክን ከመመስረቱ በላይ ታላቅ መስጊድ በ[[ኤሪዱ]]ም እንዳሰራ ይተረታል።
 
[[ዴቪድ ሮኅል]] የሚባል አንድ የ[[ታሪክ]] ሊቅ የኤንመርካርና የ[[ናምሩድ]] ተመሳሳይነት አመልክቷል። «-ካር» የሚለው ክፍለ-ቃል በሱመር ቋንቋ ማለት «አዳኝ» ነው። ኡሩክ ከተማ የተመሠረተ በኤንመር-ካር ነበር ሲባል፣ ደግሞ ናምሩድ፣ አዳኝ፣ በ[[ኦሪት ዘፍጥረት]] ምእራፍ 10 ዘንድ ኦሬክን ሰራ። በሌላ ትውፊቶች ዘንድ ይህ ናምሩድ [[የባቢሎን ግንብ]] መሪ የሆነ ነበር። በተጨማሪም አቶ ሮህል የኤሪዱ መጀመርያ ስም «ባቤል» እንደ ነበር ያምናል፤ እዚያም የሚገኘው የግንብ ፍረስራሽ የባቢሎን ግንብ ፍርስራሽ መሆኑን ገመተ።