ከ«ዒዛና» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
Luckas-bot (ውይይት | አስተዋጽኦ) ጥ ሎሌ መጨመር: hu:Ezana |
ጥ ሎሌ ማስተካከል: it:Ezanà di Axum; cosmetic changes |
||
መስመር፡ 1፦
'''ዒዛና''' (በ[[ግሪክ (ቋንቋ)|ግሪክ]]፡ '''ኤይዛናስ''')፣ ንጉሥ (ወደ 4ኛው ክ/ዘ አጋማሽ ዓ.ም.)፣ ከ[[አክሱም]] ነገስታት ሁሉ ገናና የሆነ የመጀመሪያው ክርስትያን ንጉሥ ነበር። ምናልባት ለአባቱ ለንጉሥ [[ኢላ-አሚዳ]]፡ የበኩር ልጁ ሳይሆን አይቀርም። ስለ እናቱ ሥም የሚናገር [[ታዓማኒ]] የጽሑፍ መረጃ እስካሁን ድረስ አልተገኘም። ከሁለተኛ ደረጃ ምንጮች መሠረት ግን የእናቱ ሥም [[ሶፍያ]] ይባላል። ሁለቱ ወንድሞቹ [[ሣይዛና]] እና [[ኃደፋ]] በአስተዳደር እና በውትድርና ሥራዎች ይረዱት ነበር። በተለያዩ ጊዜያት ባደረጋቸው ተከታታይ የግዛት ማስፋፍያ ዘመቻዎች፡ ንጉሥ ዒዛና ግዛቱን በስሜን [[ቤጃ]]ዎች፣ [[ካሡ]]ና [[ኖባ]] በተባሉ የተከዘ ቀበሌዎች፣ በ[[አትባራ]] እና በ[[አባይ ወንዝ (ናይል)|አባይ]] ወንዞች ፣ በምስራቅ በኩል በ[[አግወዛት]]፣ በደቡብ [[ስራኔ]] በተባለ የአፋን ምድሮች ላይ ወረራ እንደፈጸመ በ[[ግዕዝ]]፣ በጥንታዊ [[ዐረብኛ]]፣ እና በ[[ግሪክ (ቋንቋ)|ግሪክ]] ተጽፈው በ[[አክሱም]] የተገኙ የጽሑፍ መረጃዎች ያመለክታሉ። የግዛት ማስፋፍያ ዘመቻዎቹ ቅደም ተከተል ግን እስካሁን አከራካሪ ናቸው። ንጉሥ ዒዛና ከሚጠቀሱለት የአስተዳደር ባሕርያት ውስጥ፤
በንጉሥ ዒዛና ዘመን፡ አክሱማውያን በዓለም-ዓቀፍ ንግድ ረገድ እንደ ዝሆን ጥርስ፣ ወርቅ፣ የዔሊ ክዳን፣ ቆዳ፣
በንጉሥ ዒዛና ዘመን ዋንኛው ተጠቃሽ ክስተት [[ክርስትና]]ን ከ[[ፍሬምናጦስ]] አምኖ መቀበሉ ነው። ሆኖም የክርስትና እምነት ወደ [[ኢትዮጵያ]] በ 4ኛው ክ/ዘ የመጀመሪያ ዓስርተ ዓመታት ውስጥ ቀደም ብሎ መግባት ጀምሮ ነበር። በቅድመ ክርስትና ዘመኑ፡ ንጉሥ ዒዛና [[አስቴር]]፣ [[መድር]]፣ [[ቤኄር]]፣ [[ሜኅረም]]፣ [[አረስ]] በተባሉ አማልክት ያምን እንደነበረና እራሱንም የነዚህ አማልክት ልጅ አድርጎ ይቆጥር እንደነበር በጽሑፍ የተገኙ መረጃዎች ያሳያሉ። በኋለኛ ዘመኖቹ ደግሞ የአሃዳዊ መለኮታዊ አምላክ አማኝ ስለመሆኑ የሚመስክሩ ጽሑፎች ተገኝተዋል። በ 1969 በተገኘ የመረጃ ሰነድ ላይ፡ ንጉሥ ዒዛና በግልፅ ክርስትያን ስለመሆኑ ሳያሻማ ይናገራል። በዘመኑ የተቀረፁት ሳንቲሞቹ ላይ የጨረቃና-ኮከብ የቅድመ ክርስትና ምልክቶች ቀስ በቀስ፡ የመስቀል ምልክቶች ባላቸው ሳንቲሞች እየተተኩ ሄደዋል። እንዲሁም የአርያኖች ንጉሥ [[ቆንስጣንጢኖስ]] (337-361) የላከው «ለተወደዱት ሁለት ወንድሞቼ ዒዛና እና ሳይዛና፡ የአክሱም ነገስታት» በማለት የሚጀምረው ታሪካዊ ደብዳቤ ስለ ፍሬምናጦስ ጵጵስና እና ዕውቅና ጉዳይ በሚመለከት ግለስቡን ወደ [[እስክንድርያ ፓትርያርክ]] [[አትናቴዎስ]] ዘንድ እንዲልኩት የሚጠይቀው ይህ ደብዳቤ እንደ ተጨማሪ መረጃ የሚያገለግል ስነድ ነው። ፍሬምናጦስን ከዚሁ ደብዳቤ መላክ ሃያ አምስት ዓመት ቀደም ብሎ በኢትዮጵያ ጳጳስ አድርጎ ሾሞ የላከው ይኸው ንጉስ አትናቴዎስ ነበር።
መስመር፡ 7፦
በነገስታት ዝርዝር ላይ የንጉሥ ዒዛና ሥም አለመታወቁ ያስገርማል። ሆኖም በሳንቲሞቹ ላይ ያለው ሥምይኸው «ዒዛና» የሚለው ነው ያለው። በዘልማድ እንደሚነገረው ግን፡ ንጉሥ [[አብርሃ]] እና ወንድሙ [[አጽብሃ]] ክርስትና ወደ ኢትዮጵያ በገባበት ዘመን ኢትዮጵያን የሚገዙ ወንድማማች ንጉሦች ነበሩ። ምናልባት ክርስትናን በተቀበሉበት ጊዜ የወስዱት የክርስትና ሥማቸው ሊሆን ይችላል።
ስለ ንጉሥ ዒዛና ዘመነ ንግስ ፍፃሜ ወይም ስለ አሟሟቱ የሚዘረዝር ተጨባጭ መረጃ እስካሁን አልተገኘም። በአፈ-ታሪክ መረጃዎች መሠረት ግን ንጉሡ
== ምንጭ ==
* ዲክሽነሪ ኦፍ ኢትዮጵያን ባዮግራፊ፣ ቮልዩም 1፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢትዮጵያ ጥናት ማዕከል፣ 1975 (በእንግሊዘኛ የታተመ)
[[መደብ:የኢትዮጵያ ታሪክ]]
መስመር፡ 22፦
[[he:עזנה, קיסר אקסום]]
[[hu:Ezana]]
[[it:
[[nl:Ezana]]
[[pt:Ezana]]
|