ከ«ራስ መኮንን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
robot Modifying: fr:Mekonnen Wolde Mikael
ሎሌ ማስተካከል: fr:Mekonnen Welde Mikaél; cosmetic changes
መስመር፡ 1፦
[[Imageስዕል:Ras Mäkonnen (Wäldä-Mika'él) (1852-1906).jpg|thumb|right|250px|ልዑል ራስ መኮንን ወልደሚካኤል]]
 
<font size="+1">'''ልዑል ራስ መኮንን''' </font>የ[[ሸዋ]] ንጉሥ የነበሩት የ[[ሣህለ ሥላሴ]] ልጅ የ[[ልዕልት ተናኘወርቅ]] እና የደጃዝማች ወልደሚካኤል ልጅ ናቸው። ግንቦት 1 ቀን 1844 ዓ.ም ጎላ ወረዳ ደረፎ ማርያም በሚባል ሥፍራ ተወልደው፤ እስከ 14 ዓመት ዕድሜያቸው ከአባታቸው ጋር ከኖሩ በኋላ ያጐታቸው የ[[ንጉሥ ኃይለ መለኮት]] ልጅ [[ዳግማዊ ምኒልክ]] ገና የሸዋ ንጉሥ እንደነበሩ፡ ወደርሳቸው ቤተመንግሥት መጥተው፡ ባለሟል ሆኑ።<br />
በ1868 ዓ.ም ዕድሜያቸው 24 ዓመት ሲሆን ከ[[ወይዘሮ የሺ እመቤት]] ጋር ተጋብተው [[ሐምሌ]] 16 ቀን 1884 ዓ.ም የወደፊቱን [[ንጉሠ ነገሥት]] [[ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ]]ን ወለዱ።<references/>
 
ልዑል ራስ መኮንን የንጉሠ ነገሥቱ [[ዳግማዊ ምኒልክ ]] ተወካይ ሆነው ሁለት ጊዜ የ[[አውሮፓ]]ን አገሮች ጎብኝተዋል። በዚህ ጊዜ እሳቸው [[ጣልያን|ኢጣሊያ]]ን ሲጎበኙ በነበረ ጊዜ የኢጣሊያ ጋዘጦች የ[[ውጫሌ ውል]]ን በተመለከተ፤ "...በውጫሌ ውል ላይ ኢትዮጵያ የኢጣሊያን ጥገኝነት ተቀብላ ውል ከፈረመች በኋላ የ[[ጀርመን]] ንጉሠ ነገሥት ከ[[ኢትዮጵያ]] የሚላከውን ማንኛውንም ደብዳቤም ሆን ጉዳይ በኢጣሊያ መንግሥት በኩል መቀበል ሲገባቸው በቀጥታ ከምኒልክ የተጻፈውን ደብዳቤ ተቀብለዋል..." እያሉ የጻፉትን ራስ መኮንን ተቃውሞአቸውን ለኢጣሊያ መንግሥት ከነገሩ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ የውሉን መበላሸት ለአጤ ምኒልክ አሳወቁ። <references/>ከኢጣሊያንም ጋር በተደረገውም ጦርነት ራስ መኮንን 15000 እግረኛ ወታደሮች ይዘው ከምኒልክ እና ታላላቅ ጦር አዛዦች ጋር ዘምተዋል።
 
በ1898 ዓ.ም መጀመሪያ ላይ በብርቱ ስለታመሙ ለኅክምና ወደ [[አዲስ አበባ]] ለመሄድ ጥር 4 ቀን ከከተማቸው ከ[[ሐረር]] ተነሱ። [[ጥር ]] [[9]]ቀን ቡርቃ ወንዝ አድረው የ[[ጥምቀት]]ን በዓል አክብረው ከዋሉ በኋላ ሕመሙ ስለጸናባቸው ወደ ኋላ ተመልሰው ቁልቢ ገብተው በሐኪም ይታከሙ ጀመር። እዚሁም ሲታመሙ ከቆዩ በኋላ [[መጋቢት ]] 13 ቀን 1898 ዓ.ም ቁልቢ ላይ አርፈው ሐረር ላይ እሳቸው በተከሉት በ[[ቅዱስ ሚካኤል]] [[ ቤተ ክርስቲያን]] ተቀበሩ።<references/> ዐፄ ምኒልክም የአርባቸው ለቅሶ የሚለቀሰው [[አዲስ አበባ]] እንዲሆን ባዘዙት መሠረት፤ [[ሰኞ]] [[ሚያዝያ]]22 ቀን በአዲስ አበባና በዙሪያው ያሉት የየገዳማቱና የየአድባራቱ ካህናት የ[[ክርስቲያን]] የፍታት ጸሎት ተድርጎ በማግስቱም [[ማክሰኞ]] የ[[ጊዮርጊስ]] ዕለት ሚያዚያ [[23]]ቀን 1898 ዓ.ም በሰኢ ሜዳ ላይ ድንኳን ተተክሎ፤ መኳንንቱና ሠራዊቱ ተሰብስቦ የራስ መኮንን የማዕረግ ልብሳቸውና የራስ ወርቃቸው፤ ኒሻኖቻቸውና የጦር መሳሪያቸው ተይዞ ፈረስና በቅሏቸው በወርቅ እቃ ተጭነው በሠራዊቱ መካከል እየተመላለሱ ታላቅ ልቅሶ ተለቀሰላቸው። ከአልቃሾቹም አንዱ ደግነታቸውን ለማስታወስ እንዲህ ብሎ አሟሸ፤- ስልከኛው ሲያረዳ ነገር ተሳሳተው፤ መኮንን አይደለም ድኃ ነው የሞተው
 
 
 
 
== ዋቢ መጻሕፍት ==
* ''ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ - ቀ.ኃ.ሥ 1929ዓ.ም - ገጽ 1፣ 2፡ 9-10
* ''አጤ ምኒልክ - ጳውሎስ ኞኞ 1984 ዓ.ም ገጽ 143፤ 160
 
[[መደብ:የኢትዮጵያ_ሰዎችየኢትዮጵያ ሰዎች]]
[[መደብ:የኢትዮጵያ ታሪክ]]
 
[[en:Ras Makonnen]]
[[fr:Mekonnen WoldeWelde MikaelMikaél]]
[[he:מקונן וולדה]]
[[pl:Ras Makonnen]]