ከ«ፍኖተ ሰላም» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 1፦
ፍኖተ ሰላም በ[[ጎጃም]] እምብርት ላይ የምትገኝ ውብ ከተማ ናት። ፍኖተ ሰላም ማለት መልካም መንገድ ወይም ጉዞ እንደማለት ሲሆን ይህንንም ስም ያወጡላት [[ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ]] እንደሆኑ ይነገራል። ጃንሆይ ከጣሊያን ጦርነት በሁዋላ ከስደት ወደሃገር ሲመለሱ አሁን ፍኖተ ሰላም ያለችበት ቦታ ላይ ከአጃቢዎቻቸው ጋር እረፍት ያደርጋሉ። እስከዚያን ጊዜ ድረስ ያደረጉት ጉዞም በሰላም የተሞላ ስለነበር ያንን ቦታ ፍኖተ ሰላም ብለው ሰየሙት። ከከተማዋ ወጣ ብሎ የሚገኝ አንድ የዋንዛ ዛፍ ይገኛል። ይህንንም የዋንዛ ዛፍ የተከሉት ንጉሱ ስለንበሩ እስካሁን ድረስ የአባ ንጉስ ዋንዛ እየተባለ ይጠራል።
 
ፍኖተ ሰላም (ፍ/ሰላም) በብዙ ነገር ትታወቃለች። በአካባቢው ያሉ ገበሬዎች ጤፍ፣ በቆሎ፣[[በቆሎ]]፣ ዳጉሳ፣ ኑግ፣ በርበሬ እና ሌሎቹንም የእህል አይነቶች ያበቅላሉ። በፍራፍሬ ሎሚ፣ ብርቱካን፣ ፓፓዬ እንደልብ ይገኛል። በጣም ጥራት ያለው ቡና የሚገኝባት አገር ናት - ፍ/ሰላም። የባከል ቡና በጣዕሙ ይታወቃል። ከከተማው ወጣ ብሎ የገራይ የውሃ ግድብ ስለሚገኝ በተለይ በፆም ጊዜ እጅ የሚያስቆረጥም አሳ ይገኛል። ፍ/ሰላም በወተትና በማር ሀብትም በጣም የታውቀች ትንሽና ውብ ከተማ ናት።