ከ«ኅሩይ ወልደሥላሴ (ብላቴን ጌታ)» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 1፦
[[Image:Heruyjapan2.jpg|right|300px]]
 
'''ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ''' በ[[ኢትዮጵያ]] መኻል አገር በሰሜን [[ሸዋ]] [[በመርሐ ቤቴ]] አውራጃ በታች ቤት ወረዳ ረመሸት ቀበሌ ደን አቦ ገዳም በተባለ ሥፍራ በ ፲፰፻፸፩ ([[1871|፲፰፻፸፩]]) ዓ.ም ተወለዱ። ሲወለዱ የተሰጣቸው ስም ገብረመስቀል ነበር። በቤተ ክህነት ትምህርት እንጦጦ ራጉኤል ደብር መጥተው የመጻሕፍትን ትርጓሜ በዘመኑ ከነበሩት የደብሩ ሊቃውንት ዘንድ ተምረው አጠናቀዋል። እዚህ ነው አንዱ መምህራቸው «አንተ የቀለም ቀንድ ስለሆንክና በምግባርህም የተመሰገንህ ነህና፡ ኅሩይ የተባለውን ስሜን ሸልሜያሃለሁ፡ ከንግዲህ ኅሩይ እየተባልክ ተጠራ!» አሏቸው። <ref>''የኢትዮጵያ ታሪክ፡ ከንግሥተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል'' በብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ - ፲፱፻፺፱ ([[1999)|፲፱፻፺፱]] ዓ.ም</ref>
 
ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ 21ሃያ አንድ መጻሕትን የደረሱ ሲሆኑ፤ የመጨረሻው መጽሐፋቸው ''የኢትዮጵያ ታሪክ፡ ከንግሥተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል'' ለመጀመሪያ ጊዜ በ ፲፱፻፺፱ ([[1999]]) ዓ.ም የልጅ ልጃቸው ወይዘሮ ሠናይት ተክለማርያም አሳተሙት። ደራሲው ፋሽሽት [[ኢጣልያ]] ኢትዮጵያን በወረረ ጊዜ ከ[[ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ]] ጋር አብረው ወደ [[እንግሊዝ]] አገር ስደት ላይ እንዳሉ በ ስልሳ ዓመታቸው [[መስከረም 9|መስከረም ፱]] ቀን ፲፱፻፴፩ ([[1931|፲፱፻፴፩]]) ዓ.ም. አረፉ።
 
ሥርዓተ ቀብራቸው መስከረም ፲ ቀን እዚያው እንግሊዝ አገር ሲፈጸም ንጉሠ ነገሥቱ የሚከተለውን ንግግር አደረጉ።