ከ«ጉታውያን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
አዲስ ገጽ ፈጠረ፦ «'''ጉታውያን''' ከሜስጶጦምያ በላይ ባሉት ተራሮች «ጉቲ» ወይም «ቁቲ» በተባለ ሀገር የመጣ ሕዝብ ነበ...»
(No difference)

እትም በ19:57, 7 ሴፕቴምበር 2009

ጉታውያንሜስጶጦምያ በላይ ባሉት ተራሮች «ጉቲ» ወይም «ቁቲ» በተባለ ሀገር የመጣ ሕዝብ ነበረ። በ2150 ክ.በ. ገደማ የአካድ መንግሥት በወደቀበት ዘመን ወርረው የሱመር አለቆች ሆኑ።

ጉታውያን በሜስጶጦምያ ጽሕፈቶች ዘንድ ኋላቀርና ሥልጣኔ የናቀ ሕዝብ ይመስላሉ። ከነገስታታቸው ስሞች በቀር፣ ስለ ቋንቋቸው ጸባይ አንዳችም ነገር ዛሬ አይታወቅም።

መጀመርያ በታሪክ መዝገብ የሚታዩ፣ ለአዳብ ንጉሥ ለሉጋል-አኔ-ሙንዱ መንግሥት ግብር ከሚከፍሉ ሕዝቦች መካከል ሲዘረዝሩ ነው። በጽላት መዝገብ ዘንድ አገራቸው ከሹቡር ደቡብና ከኤላም ስሜን ይገኛል። በአካዳውያንም ዘመነ መንግሥት፣ ለንጉሥ 1ኛ ሳርጎን ተገዥ ሁነው ከሉሉቢ ብሔር አጠገብ ነበሩ።

የአካድ መንግሥት ድካም ለመሆን ሲጀምር፣ ጉታውያን በሜስጶጦምያ ላይ ብዝበዛ ያድርጉ ነበር። ሠራዊት እንደ ደረሰባቸው ግን ሸሽተው ነበር። ከቤት ማለፍ ወይም እንኳን በእርሻ መግባት አስጊ ሁኔታ ስለ ሆነ፣ የሜስጶጦምያ ምጣኔ ሀብት ተበላሸና ራብ ሆነ። በመጨረሻ፣ ጉታውያን አካድን ወረሩና ገዙት። እንዲሁም የጉቲ ሠራዊት ኦሬክንና ኤላምን የዛኔ ወረሩ። የጉታውያን ንጉሥ ኤሪዱፒዚር እራሱን እንደ አካድ ነገስታት በማምሰል፣ ማዕረጉ 'የጉቲ ንጉሥና የ4 ሩቦች ንጉሥ' ተባለ።

በ2050 ክ.በ. ያሕል፣ የኦሬክ ንጉሥ ኡቱ-ኸንጋል የጉታውያን ንጉሥ ቲሪጋንን እንዳሸነፈ ጉታውያንንም ከአገራቸው እንዳስወጣ ይባላል።

በኋለኛ ዘመን፣ በአሦር መንግሥት 'ጉቲ' የሚለው ስም ለሜዶን ይጠቅም ነበር። በፋርስም ንጉሥ ቂሮስ ዘመን፣ ታዋቂ አለቃ ጉባሩ 'የጉቲ አገረ ገዥ' ተባለ። በተራሮቹ የሚገኘው የዛሬው ኩርድ ሕዝብ ከጉቲዎቹ እንደ ተወለዱ የሚያምኑ ብዙ ናቸው።